Friday, October 18, 2013

ጠ/ሚኒስትሩ ተቃዋሚዎችን “ይሄ መንግስት ፈርቷል እያላችሁ ራሳችሁን አታሞኙ” አሉ


ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚ ሀይለማርያም ዛሬ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ መንግስት የጎዳና ላይ ነውጥ ከሚያሰቡት ሀይሎች ጋር ለመነጋገር የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።Thumbnail
አቶ ሀይለማርያም በተቃዋሚዎች በኩል የሚቀርበው ቅጥ ያጣ ፍረጃ እና የጥላቻ ፖለቲካ እንዲቆም  እንዲሁም የጎዳና ላይ ነውጥ እናደርጋለን በማለት የሚያስቡ ሀይሎችም ሀሳባቸውን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል። “የጎዳና ላይ ነውጥ ለማስነሳት በቂ መረጃ አለን ስንል “መንግስት ፈርቶ ማስፈራራት ጀመረ” እንባላለን ያሉት አቶ
ሀይለማርያም፣ ይህ መንግስት አይፈራም፣ ታሪኩም ባህሪውም እንደዛ አይደለም ብለዋል። ይህ መንግስት ፈርቷል እያላችሁ እራሳችሁን አታሞኙ፣ መንግስት አይፈራም የህዝብ መንግስት ነው ፣ ኳሱ እናንተ እጅ ላይ ነው” ብለዋል

No comments:

Post a Comment