Thursday, October 31, 2013

የጉዲፈቻ ልጃቸውን የገደሉ ተፈረደባቸው


ኣንዲት የጉዲፈቻ ልጃቸውን ኣሰቃይተው ለሞት ያበቁ ባልና ሚስት አሜሪካውያን ከ28 እስከ37 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተፈረደባቸው።

gudifecha
የ13 ዓመትዋ ሐና ዊሊያምስ ህይወቷን ያጣችዉ በጎርጎሪዮሳዊዉ የዘመን ቀመር ግንቦት 12 ቀን 2011 ሲሆን ከትናንንት በስተያ ማክሰኞ ዕለት ያስቻለው የሲኣትል ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ ሚስት ወ/ሮ ካሪ ዊሊያምስ 37 ዓመት እና ባል ላሪ ዊሊያምስ ደግሞ 28 ዓመት እንዲታሰሩ ፈርዶባቸዋል።
ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ኣንድ ሌላ እትዮጵያዊ የጉዲፈቻ ልጅን ጨምሮ ስድስት አብራካቸዉ የተገኙ ልጆችም ኣሏቸው።

አሳዛኝ ዜና -በጀርመን ህክምና እየተከታተለ የሚገኘው ኮሜዲያን አብርሐም አስመላሽ አረፈ።


የዲስክ መንሸራተት አጋጥሞት በጀርመን ህክምና እየተከታተለ የሚገኘው ኮሜዲያን አብርሐም አስመላሽ አረፈ።

ነፍስ ይማር

የኢዴፓ_ገበና_ሲገለጥ (ሊነበብ የሚገባው ደባ)


የልደቱ_አያሌው_ኢዴፓ_በየትኛው_ሞራሉ_ነው_ተቃዋሚውንም_ይሁን_ገዢውን_ፓርቲ_የሚተቸው??

የአቶ ልደቱ አያለውን መጽሃፍ የጻፈው በወያኔ ልዩ ትእዛዝ አቶ
ገነነ አሰፋ ነው።
ዶክተር በየነ ጴጥሮስ እና ሻለቃ አድማሴ መላኩ በአቶ መለስ ትእዛዝ የወር ደምወዝ ነበራቸው።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በኢዴፓ ህልውና አያምንም። ዘላለም ህዝቡ ኢዴፓን በበጎ መንፈስ አያየውም። በአሁን ሰአት ለተፈጠረው ኢህአዴጋዊ አክራሪነት እና የፖለቲካ ጽንፈኝነት ተጠያቂው ኢዴፓ እና አመራሩ ናቸው። ኢዴፓ ብሎ ራሱን የሚጠራው በኢሕኣዴግ የጎለበተው ድርጅት ባካሄደው ስብሰባ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን እና ገዢውን ፓርቲ እንደተቸ እየሰማን ነው። ኢዴፓ የ97 ምርጫ የህዝብን ድምጽ አፈር የከተተ እና ከገዢው ፓርቲ ጋር መሰሪ ተግባራትን በማከናወን የቅንጅት አመራርን ለእስር ቅንጅትን ደግሞ አላማውን በማኮላሸት ድባቅ እንዲመታ ያደረገ ታማኝ ቅጥረኛ በራሱ አጠራር ተቃዋሚ ፓርቲ ነው።

እረፍት የሚነሳው ህምም


የኮንትራት ሰራተኞች ስቃይ፣ የእኛ ፍርሃትና የፖለቲከኞች ጭካኔ

saudi 1


እረፍት አደርግ ብየ ከማህበራዊ መገናኛ መድረኩ ገለል ባልኩባቸው እንደ ብርሃን ፍጥነት በሚወረወሩት ባለፉት ጥቂት ቀናት ከበርካታ ወዳጆቸ በርካታ መልዕክቶች ይደርሱኛል። ብዙው መልዕክት ደግሞ የሚያጠነጥነው በጅዳ እና በአካባቢው በተፈናቃይ የኮንትራት ሰራተኞች አሰቃቂ ስቃይ ላይ ያተኮራል … ለነገሩ የአብዛኞቹ መልዕክቶች ብቻ ሳይሆኑ ከመልዕክቶች ጋር የሚላኩልኝ መረጃዎች እረፍት የሚነሱ ናቸው! …

Wednesday, October 30, 2013

ፉዓድ ኢብራሂም ዳግም ዋሊያዎቹን ተቀላቀለ


የቀድሞው የአሜሪካ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ተጨዋችና ኢትዮጵያዊ የዘር ሀረግ ያለው ፉዓድ ኢብራሂም ዛሬ ዋሊያዎቹን ተቀላቀለ፡፡

“ትግራይ ከአንድ ፋብሪካ እንደወጣ ሳሙና”


 ዛሬ አንድ ታሪክ ያስታወሰኝ አስተያየት አነበብኩ። በ97 ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩ። በኢህአዴጎችና ቅንጅቶች መካከል የነበረ ክርክር እከታተል ነበር። የማናቸው ደጋፊ ወይ ተቃዋሚ አልነበርኩም። አንድ ሲኔራችን ነበር። ሁሌ ወደ ዶርማችን እየመጣ ስለነዚህ የቅንጅት መሪዎች መጥፎ ታሪክ ይነግረናል፤ ለትግራይ ህዝብ መጥፎ አመለካከት እንዳላቸው (እንዲህ አደረጉ፣ እንዲህ አሉ እያለ)፣ የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣናት የነበሩና ወንጀለኞች መሆናቸው ወዘተ።

የቦሌ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን የድረሱልኝ ጥሪ አሰማች


 

ኢሳት ዜና :- የቦሌ ለሚ ቅ/ሩፋኤል የጻዲቁ አቡነ ኤዎስጣቲዎስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ብርሀን ተከስተ ካሳሁን “የድረሱልን ጥሪን ይመለከታል” በሚል ርእስ ለለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብጹዕ ወቅዱስ ፓትሪያርክ ረዳትና የጅማ ሀገረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ለሆኑት ለ ብጹዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጻፉት ደብዳቤ ላይ፣ የመንግስት ባለስልጣናት ቤተክርስቲያኑዋን በ7 ቀናት እንዲያፈርሱ እንዳዘዙዋቸው ተናግረዋል።

የኢትዩ ምህዳር አዘጋጆች አደጋ ደረሰባቸው


ዛሬ ሐዋሳ ፍርድ ቤት ለመቅረብ ትናንት ምሽት ወደ ስፍራው ያመሩት የኢትዩ ምህዳር ሶስት ጋዜጠኞች ማለዳ ላይ በሲዳማ ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ይመለከቱ የነበሩት ዳኛ ለከሰዓት 9፡00 ሰዓት እንዲቀርቡ ይነግሯቸዋል፡፡ጋዜጠኞቹ ጊዜውን በከንቱ ላለማባከን በማሰብ በሐዋሳ ዜና ፍለጋ ይሰማራሉ፡፡

Tuesday, October 29, 2013

ዋሊያዎቹ ለወሳኙ የናይጄሪያው የመልስ ጨዋታ ልምምዳቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል


- ጌታነህ ከበደ በቀጣዩ ወሳኝ ጨዋታ ሊሰለፍ ይችላል

- “በቡድኑ ውስጥ የማሸነፍ መንፈስ አለ” – ደጉ

ከቦጋለ አበበ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ባለፈው ጥቅምት ሦስት በሜዳቸው ሽንፈት ከደረሰባቸው በኋላ ቀጣዩን ጨዋታ በድል ለመወጣት ዝግጅታቸውን ጀምረዋል። ከሳምንት በፊት ልምምዳቸውን የጀመሩት ዋልያዎቹ በቀጣዩ ጨዋታ በሜዳቸው የገጠማቸውን ሽንፈት ለመቀልበስ ያስችላቸው ዘንድ ጠንካራ ልምምድ እየሠሩ ይገኛሉ።

የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ አስተዳደር ከተማሪዎች አመጽ ጀርባ ኢሳት እና ሌሎች ሀይሎች እንዳሉበት ገለጸ


ኢሳት ዜና :- ተማሪዎች የርሃብ አድማ በማድረግ ላይ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲው ትክክለኛነቱን አረጋግጦዋል፡፡
የተማሪዎች አመጽ የተነሳው መንግስት ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አዲስ የአለባበስ ፤ የአመጋገብ እና የአምልኮ ስርዓት ህግ ማውጣቱን ተከትሎ ነው። ” ተማሪዎች እምነታችሁ ተው ፣ ማተባችሁን በጥሱ” ተብለናል ይላሉ።

Monday, October 28, 2013

የኢትዮጲያ ወዳጆች በሙሉ እንዲገኙ የከበረ ጥሪ እናቀርባለን


በቅርቡ ከኢትዮጲያ ኦጋዴን/ሶማሌ ክልል በድብቅ ወጥቶ በስዊዲን ቴሌቪዥን የተላለፈው ዶክመንተሪ ፊልም የዓለም ህብረተሰብን ያስደነገጠና ያስቆጣ በመሆን የወያኔን አረመኔአዊ አገዛዝ በድጋሚ አጋልጧል ።

“ከ40 ግድብ አንድ የቀይ ባሕር ወደብ!


ክፍሉ ሁሴን

“ከ40 ግድብ አንድ የቀይ ባሕር ወደብ!”የኢትዮሚዲያ ድረገጽ የወቅቱ መፈክር ነው።ከመፈክሩ ጋር ወይም በመፈክሩ ላይ ምንም ችግር የለብኝም።ይልቁንም ወያኔ ከሌሎች ክፉ ነገሮች በተጨማሪ ወደባችንን አስበልቶ በምድር ብቻ ተቀርቅበን የቀረን አገር ስላደረገን እስከ ዛሬ ድረስ ከሚንገበገቡት ኢትዮጲያውያኖች አንዱ ነኝ።የባሕር በር ባለቤትነታችን በእኔ እድሜ እንኳ ባይመለስ ቢያንስ የባሕር በር እንድናጣ ባደረጉን ዋና ዋና ከሃዲዎች ላይ በአገር ክህደት ወንጀል ክስ ሲመሰረት በሕይወት ዘመኔ ለማየት ከፍተኛ ጉጉት አለኝ።በነገራችን ላይ በዚህ ክስ በቀንደኛነት እንዲካተቱ ከምፈልጋቸው ሰዎች ውስጥ አንዱ መንግስቱ ኃይለማሪያም ወልዴ ነው።ስለምን?በዋናነት የተበላነው እሱ የ”አብዮታዊ ጦር ጠቅላይ አዛዥ”በነበረ ጊዜ ነውና።

አደባባዩ ምን ያህል ይርቃል? – ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ


እነሆ ይቺ ሀገር ኢትዮጵያ ናትና የመብት (የለውጥ) ጥያቄዎች፣ እንደ አህጉር ተጋሪዎቿ ሁሉ መልስየሚያገኙት ከአደባባይ ጩኸት ብቻ ይሆን ዘንድ ባህል ሆኖአል፡፡ ትውልድ ተሻጋሪ ታሪኳም የሚነግርህ  በየወቅቱ ከተፈራረቁ ገዥዎቿ አንዳቸውም እንኳ ለህዝብ ፍላጎትና ውሳኔ ተገዝተው አለማወቃቸውን ነው፤ ጠመንጃ አሊያም ተፈጥሮ ወደ ግብአተ መሬት ካልሸኛቸው በቀር፡፡ የሩቁን (የጨለማውን ዘመን) ትተን፣ የቅርቡን እንኳን ብንመለከት በወጡበት መንገድ፣

የአድዋዉ ልጅ አድዋ ገባ” የአርማጭሆ ልጅ የት ይግባ?!! (ናደዉ ከዋሽንግተን ዲሲ)


የአድዋዉ ልጅ አድዋ ገባ”
የአርማጭሆ ልጅ የት ይግባ?!!
እንደምን ከረማችሁ ዉድ የኢካዴፍ እድምተኞች “እስቲ ቂማችንን ጥቂት እናቆየዉ” በሚል ርእስ የጀመርኩትን መጣጥፍ “በአሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል” ቀጥዪ ከክፍል 1-7 ድረስ ይህ ድህረ ገፅ ለንባብ አብቅቶልኛል ክፍል 8-9 ግን ከአንድም ሁለቴ በአደራ ደብዳቤ ሳይቀር ልኬ ሚዛን ባለመድፋቱ ለንባብ አልበቃም(የቅርጫት ራት ሆኗል) ሚዛን የሚደፋ ፅሁፍ ለማቅረብ አስቤ ፅሁፎቼን ቆየት ማድረግ በወሰንኩ ማግስት ዛሬ October 24, ምሽት አንድ ወዳጄ ስልክ ደዉሎ ሰበር ዜና ጀባ አለኝ የአዉራምባዉ አምደኛ ተጋዳላይ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ወደ ዘረኛ ግብረአበሮቹ ጉያ መሸጎጡን አጫወተኝ ከላይ በጠቀስኩት ርእስ እንደጠቀስኩት ይህ ሰላይ የትግራይ ጉጅሌ መልእክተኛ አዚህ ሰሜን አሜሪካ ኢሳትንና ሌሎች ጠንካራ ናቸዉ የሚባሉትን ተቃዋሚ ድርጅቶች የመሰለል ተልእኮዉን አጠናቅቆና የዳያስፖራዉን ተቃዋሚ ጓዳ ጎድጓዳ ሰልሎ የቃረማቸዉን የኦዲዮ ቪዲዮና ዳጎስ ያለ ጥራዝ ተሸክሞ አሜሪካ በገባበት አኳኋን ተመልሶ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በአራት ኪሎ ቤተመንግስት ገባላችሁ ቡራኬዉንም ተቀብሎ በአዲስ አበባዉ ሸራተን ሆቴል የወሬ ቅራቅምቦዉን ለህወሀት የዜና አዉታሮችና የስለላዉ መረብ ክፍል አለቆቹ እያጋታቸዉ መሆኑን ዉስጥ አዋቂ ምንጮች ሹክ አሉን።

የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች ከተለያዩ ምንጮች


“መጽሐፈ ቅዳሴ” ወደ ኦሮምኛ ተተረጎመ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን “መጽሐፈ ቅዳሴ” ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተተረጎመ፡፡ ለብዙ ዘመናት “መጽሐፈ ቅዳሴ”ን በግእዝ እና በአማርኛ ስትጠቀምበት የቆየችው ቤተክርስትያኗ፤ መፅሃፉን በኦሮምኛ ማስተርጎም የጀመረችው በ1999 ዓ.ም እንደሆነ ታውቋል፡፡ የመጽሐፉ መተርጎም በኦሮሚያ ክልል ላሉ አብያተ ክርስትያናት በኦሮምኛ ለመቀደስ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡

በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ተቃውሞ ቢያቀርቡም የኢህአዴግን ጆሮ ማግኘት ያልቻሉ ተበዳዮች ርምጃ ወሰዱ።


በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ተቃውሞ ቢያቀርቡም የኢህአዴግን ጆሮ ማግኘት ያልቻሉ ተበዳዮች ርምጃ ወሰዱ። ሕዝብ ወዶና ፈቅዶ ያልተቀበለው ኢንቨስትመንት ከዘረፋ ተለይቶ እንደማይታይ የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቀዋል። ውድመት የደረሰበት የህንድ ኩባንያ በልማት ባንክ ላይ ኪሳራ ሊያስከትል እንደሚችል ስጋት አለ። ለደረሰው ጉዳት “ተጠያቂው ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ተነስቷል። በጥርጣሬ የሚታሰሩ መበራከታቸው በክልሉ ባሉ ተመሳሳይ የእርሻ ኢንቨስትመንት ባለቤቶችን ስጋት ላይ ጥሏል።

በደረሰባት ከፍተኛ የአሲድ ጥቃት ጉዳት ደርሶባት የቆየችው ከሚላት መሀዲ እሁድ እለት የጋብቻ ስነ ስርዓቷን ፈፅማለች።


አስደሳች ዜና:

ከጥቂት አመታት በፊት በደረሰባት ከፍተኛ የአሲድ ጥቃት ጉዳት ደርሶባት የነበረው እና የህዝብ መነጋገሪያ ሆና የቆየችው ከሚላት መሀዲ በክቡር ዶ/ር መሀመድ ሁሴን አላሙዲን ድጋፍ በከፍተኛ ወጪ በፈረንሳይ ሀገር የፕላስቲክ ሰርጀሪ ሲደረግላት ቆይታ በዛሬው እለት የጋብቻ ስነ ስርዓቷን ፈፅማለች።

Sunday, October 27, 2013

የጀነራል መኮንኖች የምደባ ለውጥ ተካሄደ


ሜጀር ጀነራል አደም መሀመድ የአየር ሀይል አዛዥ ሆነው መሾማቸውንና የአዛዥ ጄነራሎች ላይም የምደባ ለውጥ መደረጉን ምንጮቻችን አመለከቱ፡፡ በአየር ሀይል አዛዥ በነበሩት ሜጀር ጀነራል ሞላ ሀይለማርያም ምትክ የተሾሙት ሜጀር ጀነራል አደም የአየር ሀይል ፓይለት የነበሩና በሱዳን አቢዬ ግዛት የሠላም አስከባሪ ሀይል ምክትል አዛዥነት ያገለገሉ እንዲሁም የመከላከያ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ነበሩ፡፡

Friday, October 25, 2013

የአውራምባ ታይምሱ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ዛሬ አዲስ አበባ ይገባል


ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ Journalist Dawit Kebede

“እጅግ አስደንጋጭ ዜና ነው” ሀገር ቤት ያሉ ጋዜጠኞች
Ethiopia Zare (ዓርብ ጥቅምት 15 ቀን 2006 ዓ.ም. Oct. 25, 2013)፦ በሀገር ቤት ይታተም የነበረው “አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ እና የድረ ገጹ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ከሁለት ዓመት በሰሜን አሜሪካ የስደት ቆይታ በኋላ በዛሬው ዕለት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚበር ገለጸ። በጉዳዩ ላይ ከአቶ ያሬድ ጥበቡ ጋር በቪዲዮ ቃለምልልስ አድረጓል።

ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነትን ሊያስር መሆኑ መረጃዎች አመለከቱ፤…


ሰማያዊ ፓርቲ በተከራየው ቢሮ ምክንያት ከፖሊስ ጋር ወዝግብ ውስጥ መግባቱ የሚታወስ ሲሆን ተከራይ ነኝ ባዩ ግለሰብ «በሩ ላይ የሰቀልኩትን ባነር በጥሰውብኛል» ብሎ ኢንጂነሩ ላይ ክስ  መስርቷል። ፖሊስም የሰማያዊን ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃልን ለማሰር እንቅስቃሴ የጀመረ መሆኑ ታውቋል። ኢ/ር ይልቃል ግን በቤተሰብ ጉዳይ ከአዲስ አበባ ውጪ መሆናቸው ተሰምቷል።

Thursday, October 24, 2013

በቤይሩት ኢትዮጵያዊቷ በመኪና አደጋ ህይወትዋ አለፈ


በቤይሩት ኢትዮጵያዊቷ በመኪና አደጋ ደርሶባት ቆንስላ ጽፈት ቤቱ ሀላፊነት አልወስድም በማለቱ መዳን ስትችል ህክምና ባለማግኘቷ ለህልፍት በቃች…

የቆንስላ ጽፈት ቤቱ ሀላፊዎች በእህቶቻችንን ላይ የሚደርሰውን ግፍና መከራ ችላ በማለት የራሳቸውን ብቻ ቢዝነስ ሲያሳዱ የበርካቶች ህይወት እንደቀልድ ያልፋል: : ፥ ቤተሰቦቻቸው ተበድረው የላኳቸው ሊጆቻቸውን እሬሳ እንደገና በብድር ሲያስገቡት ብታዮ ልብ ይሰብራል:: ከዚህ በላይ በዜጎቹ ላይ ቁማር የሚጫወት የዜጎቹ መከራ ግፍ ስካይና ጉዳት የማያሳስበው መንግስት በሀለም ላይ አለ ?

Wednesday, October 23, 2013

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ከማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አንድነት አሳሰበ:- በመስከረም አያሌው


UDJ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ካለፈው ስህተታቸው በመማር ከአጉልና ማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አሳሰበ።

ፓርቲው ከትናንት በስትያ ባወጣው መግለጫ እንደገለፀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በመሪ ደረጃ በማይጠበቅ መልኩ የአንድነትን እንቅስቃሴ ስም ለማጥፋት በመሞከራቸው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የራሳቸው አጀንዳ የላቸውም፣ የሻዕቢያ መልእክት አድራሾች ናቸው ያሉት የራሳችን አጀንዳ እንዳለን ጠፍቷቸው ሳይሆን ሆን ብለውና አቅደው ስም ለማጥፋት እንዲሁም ህዝቡ ውስጥ ጥርጣሬ ለመጫር በመፈለግ ነው ብሏል።

Top 10 Richest Ethiopians in 2013


75f9c-64714_277529845721314_403137022_n

oct23,2013
Ethiopia is among the top ten poorest countries in the world.

ብረታ ብረት ኮርፖሬሽንና ሚድሮክን ጨምሮ 20 ድርጅቶች እንዳይፈተሹ ያደረጉ ከፍተኛ የሙስና ተጠርጣሪዎች ተከሰሱ


-አቶ መላኩ ፈንታ የሦስት ልጆች እናትን አፋተው አግብተዋል ተባለ
-አቶ ጌቱ ገለቴን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌሉበት ክሳቸው ተሰማ
በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ከግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. መጀመሪያ ጀምሮ በቁጥጥር ሥር ውለው ነሐሴ 22 ቀን 2005 ዓ.ም. ክስ ተመሥርቶባቸዋል የተባሉት

ስብሃት ነጋ በመርሳት ችግር (ዳመንሺያ) በሽታ ተጠቂ እንደሆኑ ተገለጸ !


(ዘ-ሐበሻ) አዛውንቱ የሕወሐት መስራች ስብሃት ነጋ በመርሳት በሽታ (ዳመንሺያ) በሽታ ተጠቂ እንደሆኑ ለአዛውንቱ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገለጹ። ምንጮች በተለያዩ ሁኔታዎች እንደገለጹት ስብሃት በየመድረኩ አንድ ጊዜ የተናገሩትን በሌላኛው ጊዜ የማይደግሙት፣ ወይዘሮ አዜብን ጨምሮ ከተለያዩ የኢሕአዴግ ሰዎች ጋር የሚላተሙት ወይም ጥያቄ ሲጠየቁ አላስታውስም የሚሉት የዳመንሺያ ተጠቂ በመሆናቸው መሆኑን የህክምና ባለሙያዎችን ጥናት ያሰባሰቡት እነዚህ ምንጮች ገልጸዋል። 

Tuesday, October 22, 2013

ተገዥነታችን ለሕዝብና ለሕግ እንጅ ለአምባገነኖች ማስፈራሪያ አይደለም!!! – ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ!!


ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ በሀገራችን ላይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሰፍንና ፍትሃዊነት እንዲኖር በቁርጠኝነት እየታገለ ይገኛል፡፡ በትግሉ ውስጥም ፓርቲያችን የተጋረጡበትን ፈተናዎች እየተወጣና የሚከፈለውን ዋጋ እየከፈለ ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ በመቀጠል ለህዝቡ ያለውን ታማኝነት እያረጋገጠም ነው፡፡

ፓርቲያችን በመላ ኢትዮጵያ ያለውን አደረጃጀት በመጠቀምና ሕዝቡን በማሳተፍ ለሶስት ወራት የሚቆይ ህዝባዊ ንቅናቄ በማካሄድ የመጀመሪያ ዙር የሆነውን ሰላማዊ ትግል ለማጠናቀቅ ችሏል፡፡ የሚልዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ አራት መሰረታዊ ጥያቄዎችንና ወቅታዊ ጉዳዮችን ያነገበ ሲሆን እንደ ሁልጊዜውም ፓርቲው ሰላማዊነቱን በጠበቀ መልኩ በቁርጠኝነት ንቅናቄውን በታቀደለት መሰረት አካሂዷል፡፡ ወደፊትም ይህንን አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን ለማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ትእምት የህወሓት ንብረት እንጂ የትግራይ ህዝብ ሃብት እንዳልሆነ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባልና የማረት ሓላፊ ኣቶ ተክለወይኒ ኣሰፋ ተናገሩ


! ……. የገዢዎቻችን ነገር ……….!


ኣንድ
በ1993 ዓም የህወሓት ክፍፍል መለስ የነ ስየ/ተወልደ ቡድን ለማሸነፍ በህወሓት ሰነፎች (የራሳቸው ነፃ ሓሳብ ያልነበራቸው) የፓርቲው ሰዎች ኣሰባስቦ ‘እኔን መርጠዋል’ ብሎ በህወሓት ሊቀመንበርነቱና የጠቅላይ ሚኒስተር ስልጣኑ ይዞ እንደሚቆይ ኣሳወቀ። ኣቶ ኣባይ ወልዱም ይሄንን ‘የመለስ ራእይ’ (ሰነፎች ማሰባሰብ፣ ጎበዞች ማባረር) እየተገበረ ይገኛል።

Monday, October 21, 2013

“ኢትዮጵያነቴን ይዤው ወደ መቃብር እሄዳለሁ” አቶ ተስፋዬ ገ/አብ


ቀደም ብዬም ተናግሬያለሁ። ማንም ሊከለክለኝ አይችልም። ማንም ሊሰጠኝ አይችልም። አገር ውስጥ እንዳልገባ ልከለከል እችል ይሆናል። የልብ ስሜቴን መንጠቅ የሚችል አንድም ሰው የለም። ይህንን ስሜቴን ነው ባጭሩ ማነገር የምፈልገው።ማንም አይቻለውም። ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቼ ሚሊዮኖች አሉ።በተለያዩ ምክንያቶች አገር ቤት መግባት አይችሉም። ከጥቂት ጊዜያት  በሁዋላ ግን እንደጎርፍ ነው ወደ አገራችን የምንገባው።ይህንን ነው ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው። / አበባ ይበተንለታል/ ለከለከሉኝ ክፍሎች ማን ነው ያ ከልካይ በመሰረቱ? ከየት ነው የመጣው? ያ ሰው ምን አደረገ ለአገሪቱ?እኔ የቢሾፍቱ ልጅ ነኝ። ኢትዮጵያዊ ነኝ። ይህንን መከልከል የሚችል ማንም የለም።ይዤው ወደ መቃብር እሄዳለሁ። እስከመጨረሻው … (ተስፋዬ ከኢካድኤፍ የመወያያ መድረክ ጋር ካደረገው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ)

ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ለሥራ መሄድ ሊታገድ ነው


ሳዑዲ ዓረቢያ በየወሩ እስከ 10 ሺሕ የቤት ሠራተኞችን ከኢትዮጵያ ትፈልጋለች

Sunday, October 20, 2013

የታሰሩት የዋልድባ መነኮሳት የት ገቡ!? (አቤ ቶኪቻው)

ዋልድባ በ1998 ዓ.ም አካባቢ ከጓደኞቼ ጋር ሆኜ፤ ለአንድ ስታስቲክሳዊ ስራ ወደ ወደ አርማጭሆ አካባቢ ሄጄ ነበር። በወሬ ደረጃ ስንሰማው የነበረ “አርበኞች ግንባር” በመባል የሚታወቅ የታጠቀ ቡድን እዚህ አካባቢ “በህይወት” መኖሩን ሰማሁ። ለስታስቲክሳዊ ስራው የገጠሩን መንደር መንገድ እንዲመሩን የተመደቡልን የመንግስት ታጣቂዎች ነበሩ። እኔ እና ሌሎች ከአዲሳባ ለስራ ወደ እዚህ የመጣን ልጆች ስለ አርበኞች ግንባር በደንብ ለማወቅ ጉጉት አድሮብናል። ነገር ግን የመንግስት ታጣቂን ስለ ተቃዋሚ ለዛውም ስለ ሸማቂ ሃይል መጠየቅ እየፈራን እየተባን በአካባቢው ስለሚኖሩ ሽፍቶች በመጠየቅ እናሟሙቅ ጀመር።
“እዚህ አካባቢ ሽፍታ አለ ይባላል እውነት ነው?”  አልነው አጃቢያችንን፤

የአስተሳሰብን ህግ ካልጠበቅን ለመግባባት ያቅተናል


ለብዙ ዓመታት የማውቀው ወዳጄ ገብሩ ታረቀኝ በፍትህ ጋዜጣ ላይ፣ የማላውቀው አቶ ዓሥራት በአድማስ ጋዜጣ ላይ በትግሬነታቸው ተቆርቁረውና እኔን ባዕድ አድርገው የጻፉትን አንብቤ ሁላችንንም የሚያውቁ ሌሎች ሰዎች አስተያየት እንዲሰጡበት በማለት መልስ ከመስጠት ተቆጥቤ ቆየሁ፤ ሆኖም እስካሁን ከአንድ ሰው በቀር የደረሰልኝ የለም፤ ስለዚህ እኔው ልጋፈጠው፡፡

ህውሃት ኢሃደግ መንግስት በልጆቼ ለምን ዘመተ? (ከኣስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል)



  1. Photo: አስገደ ገብረስላሴና በእስር እየተሰቃዩ ያሉ ልጆቹ።
ሁለተኛ ልጄ ክብሮም እንደ ወንድሞቹ የእስር ሰለባ ሆነ፡፡እኔ ለኢትዮፕያ ህዝብ ጠላት ሳልሆን ፍፁም ወዳጁ ነኝ መጀመርያ ደርግን 17 ኣመት በመታገል ፋሽሽታዊ ደርግ በማስውግድ ኣስተዋፅኦ ነበረኝ፡፡ ህውሃት ኢህኣደግ ስልጣን ከያዘ በሃላም ለንሮየ ለደሞወዝ ሳላስብ 17 ኣመት ሙሉ የታገልኩበት ኣላማ ስለተቀለበሰ በተጨማሪ የህውሓት መሪዎች ለኢቲዮፕያ ሉኣላዊነትና ኣንድነት ታማኝነት ስላጎደሉ የኢትዮፕያ ሕገመንግስት በሚፈቅደው መሰረት በግልም በፓርቲ ተደራጅቼ እየታገልኩ ቆይቼ ኣሁንም እታገላለው ታድያ እኔ በሃገራችን ሕ/መንግስት በሚፈቅድልኝ መሰረት መታገሌ እንደ ሃጠያት ተቆጥሮ የቂም በቀል ፖለቲካ ወደ ልጆቼ ምን ኣመጣው ይህ ለማለት የፈለጉኩት፡፡

በኦጋዴን የነዳጅ ጉድጉድ ቁፋሮ ተጀመረ


በኦጋዴን የነዳጅ ጉድጉድ ቁፋሮ ተጀመረ


ኒው ኤጅ የተሰኘው የእንግሊዝ ኩባንያ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኦጋዴን ቤዚን፣ ኤልኩራን በተባለ ሥፍራ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ ጀመረ፡፡ ኒው ኤጅ በኦጋዴን ብሎክ ሰባት፣ ስምንትና አዲጋላ በተባለ ድሬዳዋ አቅራቢያ በሚገኙ የነዳጅ ፍለጋ ቦታዎች አፍሪካ ኦይል ከተሰኘ የካናዳ ኩባንያ ጋር በነዳጅ ፍለጋ ሥራ የተሰማራ ኩባንያ ነው፡፡ ኩባንያው ኤልኩራን በተባለ በሶማሊያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ አካባቢ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ ጀምሯል፡፡

Saturday, October 19, 2013

ኃ/ማርያም ደሳለኝ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ አፍሪካን እንዳይዳኝ ለማድረግ እየተሯሯጠ መሆኑ ታወቀ




የወያኔዉ ጠ/ሚኒስቴርኃ/ማርያም ደሳለኝ ከጌቶቹ በተሰጠዉ መመሪያ መሰረት የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸሙትን የወያኔ መሪዎች ከተጠያቂነት ለማዳን ቀንና ማታ እየሰራ መሆኑን ጉዳዪን በቅርብ የሚከታተሉ ዘጋቢዎቻችን ዲፕሎማቲክ ምንጮችን በመጠቀስ በላኩልን ዜና ገለጹ። በኬንያ አነሳሽነት የአፍሪካ ኅብረት በቅርቡ በአዲስ አበባ ዉስጥ በጠራዉ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ የወቅቱ የኅብረቱ ሊቀ መንበር የሆነዉ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ የአለም አቀፉን የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ‹‹የአፍሪካ መሪዎችን አዳኝ ተቋም›› ብሎ ሲጠራዉ የተደመጠ ሲሆን ኃ/ማሪያም ከዚህ በተጨማሪ አለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በአፍሪካ ላይ በሚወስዳቸው ዕርምጃዎች የአፍሪካ ኅብረት በተደጋጋሚ ቅሬታውን ያሰማ ቢሆንም፣ አንድም ጊዜ አልተደመጠም የሚል ተልካሻ አስተያየት ሰጥቷል፡፡ የአፍሪካ ህብረት በእንደዚህ አይነቱ ጉዳይ ላይ በመሪዎች ደረጃ ሲሰበሰብ የመጀመሪያ ቢሆንም የኢትዮጵያ መሪዎች አለም አቀፉን የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ሲያወግዙ ግን ኃ./ማሪያም ደሳለኝ የመጀመሪያ አይደለም። የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር አል በሽር ባለበት ቦታ እጁ ተይዞ ለአለም አቀፉ ፍርድ ቤት እንዳይሰጥ ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉ የሚታወስ ነዉ።

የአይጥ ምስክር ድንብጥ እንዲሉ የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት የአስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር የሆነዉ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ‹‹የፀጥታው ምክር ቤትና ፍርድ ቤቱ በተከተሉት ‘ደብል ስታንዳርድ’ ምክንያት ኅብረቱ ያቀረባቸውን ቅሬታዎች ‘ጆሮ ዳባ ልበስ’ ብለውታል ሲል ተደምጧል፡፡ ቀጥሎም የራሱ ፓርቲ አባል የነበዉና የትግል ጓደኛዉ መለስ ዜናዊ አይኑ ፊት የአኝዋክን ህዝብ ሲጨፈጭፍ ዝም ብሎ የተመለከተዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም “ዜጐቻቸውን የሚጨፈጭፉ የአፍሪካ መሪዎችን ተቀምጠን አናይም” ብሏል፡፡ “ድምፃችን ከፍ ብሎ መሰማት መጀመር አለበት” በሚል ኃይለቃል ንግግሩን ያጠቃለለዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ የአፍሪካ ኅብረት አባል አገር መሪ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቱ መጠየቅ ፍፁም ንቀት መሆኑን ተናግሯል፡፡

የስዊድን የጦር ኮሚሽን በኦጋዴን ስለተፈጸመው ወንጀል አፋጣኝ መልስ እንደሚሰጥ አስታወቀ


ኢሳት ዜና :-በኦጋዴን የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚያሳየው ዘጋቢ ፊልም በቅርቡ በስዊድን ቴሌቪዥን መለቀቁን ተከትሎ ዛሬ አርብ፣ የስዊድን የጦር ኮሚሽን ማስረጃዎችን ተረክቧል።

ማስረጃዎችን ለኮሚሽኑ ያስረከቡት ሂደቱ ዋና ተወናይ የሆነው ወጣት አብዱላሂ የሱፍና የአለማቀፍ የህግ ባለሙያዎች ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ስቴላ ጋርደ ናቸው።
የጦር ኮሚሽኑ የቀረበለትን ማስረጃ በማየት አፋጣኝ ውሳኔ እንደሚሰጥ መግለጹን ወጣት አብዱላሂ ለኢሳት ተናግሯል።

በዘር ማጥፋት ወንጀል የተጠረጠሩ የወያኔ ባለስልጣናትን ለፍርድ ለማቅረብ የሚደረገዉ ጥረት ተጧጡፋል


ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት ጋምቤላ፤ ኦጋዴን፤ ጉራ ፈርዳ፤ ቤንሻንጉል፤ አርባጉጉና አዲስ አባባ ዉስጥ ለፈጸሙት የዘር ማጥራትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ተጠረርጠሪ የሆኑትን የዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ባለስልጣኖች ለአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ለማቅረብ የሚደረገዉ ጥረት በአዲስ መልክ ተጧጡፎ መቀጠሉን ሰሜን አዉሮፓ ዉስጥ የሚገኙ ዘጋቢዎቻችን በላኩልን ዜና ገለጹ። ኢትዮጵያ ዉስጥ በኦጋዴን ክልል የወያኔ አገዛዝ የሚፈጽመዉን የጦር ወንጀልና የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚያሳዉና በወጣት አብዱላሂ ሁሴን አማካኝነት ከኢትዮጵያ ሾልኮ ከወጣዉ ቪድዮ ጋር ተቀነባብሮ የተሰራዉ ዘጋቢ ፊልም ሲዊድን ዉስጥ በቴሌቪዥን ከቀረበ በኋላ ፊልሙን የተመለከቱ ስዊድናዉያንና ሌሎችም አለም አቀፍ ጠበቆች ጉዳዩን ወደ አለማቀፍ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እስካሁን ድረስ ያልታየ ትልቅ ንቅስቃሴ ጀመረዋል። ወጣት አብዱላሂ ለኢሳት ቴሌቪዥንና ሬድዮ በሰጠዉ ቃለመጠይቅ እንደተናገረዉ ፊልሙ በቴሌቪዥን ከተላለፈ በኋላ ሌሎች ብዙ የአገሪቱ ሚዲያዎች ሰፊ ሽፋን አንደሰጡትና ይህንኑ የተከታተሉት ስቴላም የተባሉ የ አይ ሲ ጄ ጠበቃ ጉዳዩን ፍርድ ቤት እንደሚያቀርቡት በሬዲዮ ይፋ አድርገዋል።የስዊድን የጦር ወንጀል ኮሚሽን ፍርድ ቤትም ማስረጃዎችን በመመርመር ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ ከወጣት አብዲ ጋራ ቀጠሮ ይዘዋል። ጠበቆቹ ጄኔቫ ካለው አይሲጄ ጋር እና ከሌሎችም የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን ጉዳዩን ወደ አለማቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት ለመውሰድ እንደሚሞክሩ ተናግሯል።

ቴዲ አፍሮ በማርፈዱ ሸራተን እንዳይገባ ተከለከለ


ቴዲ አፍሮ በማርፈዱ ሸራተን እንዳይገባ ተከለከለ
ሰሸዋንዳኝ የአልበም ምርቃት የተጋበዙት ሠራዊት ፍቅሬና ሰይፉ ፋንታሁንም ተከልክለዋል
በሸራተን አዲስ ጋዝ ላይት ክለብ ከትናንት በስቲያ ሰተካሄደው የድምፃዊ ሸዋንዳኝ ኃይሉ “ስጦታሽ” አልበም ምርቃት በክብር እንግድነት የተጠራው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፤ ሰዓት አርፍዶ በመድረሱ እንዳይገባ ተከልክሎ ከበር ተመለሰ፡፡

Friday, October 18, 2013

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰማች


ጥቅምት (ስድስት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትሪያርክ ስብሰባ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ባለው 32ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በቤተክርስቲያኑዋ ታሪክ  ተሰምቶ የማያውቅ ተቃውሞ ተከስቷል። አንድ በስብሰባው ላይ የተሳተፉ አባት እንደገለጹት በስብሰባው ላይ ”  ይህ መንግስት የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ለማፍረስ እንደተነሳ በስፋት ተነግሯል።

Ethiopia police 'torture and abuse' political prisoners


Thousands of Ethiopian opposition activists demonstrate in Addis Ababa on June 2, 2013 calling for government reforms and the release of political prisoners.Protests earlier this year called for the release of political prisoners

Related Stories

Ethiopian authorities are torturing and mistreating political detainees to extract confessions, Human Rights Watch says.
The US-based group says former prisoners at the main detention centre in Addis Ababa described being beaten and kicked during interrogation.

ሂውማን ራይትስ ወች – የፖለቲካ እስረኞች እንዲሰቃዩ ይደረጋል (የድምጽ ስርጭት )


የድምጽ ስክሪፕት
የቀድሞ የፖለቲካ እስረኞች ጋር የተደረገ ቃለ-መጠይቅ፤ ከመስከረም 24 – 28፣ 2006ዓ.ም ባለው ግዜ ውስጥ የተቀረጸ፡፡(ሁሉም መረጃ ያለምንም ገደብ ሊሰራጭ የሚችል ነው)
1. ላቲሽያ ባዴር የሂውማን ራይትስ ወች ሪሰርቸር ፡ ማዕከላዊ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ መሐል አዲስ አበባ ላይ የሚገኝ አንዱ ዋና የፖሊስ ጣቢያ ነው፡፡ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው በማዕከላዊ የሚገኙ አብዛኞቹ መርማሪዎች ህጋዊ የምርመራ መንገድ ሳይሆን የሚጠቀሙት ከእስረኞቹ መረጃ ለማውጣጣት ብሎም በግድ ለማሳመን እና ቃል ለመቀበል ጎጂ መንገድ ነው የሚከተሉት፤ አብዛኞቹ ጉዳዮችም እውነታነት የላቸውም፡፡ በማዕከላዊ ቀድሞ የታሰሩ እና በተለይ ደግሞ በሁለቱ የማቆያ ክፍሎች የነበሩ ያናገርናቸው የቀድሞ እስረኞች አስከፊ ሁኔታ እና አያያዝ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል፤ እስረኞቹ እንደነገሩን እና እንዳብራሩት በምርመራ ወቅት ተደብድበዋል፣ በጥፊ ተመተዋል እንዲሁም ጎጂ ቃላቶች ተሰንዝሮባቸዋል፡፡]

ኢትዮጵያ፡ በፖለቲካ እስረኞች ላይ የማሰቃየት ድርጊት ይፈጸማል


በግዳጅ የእምነት ቃል እንዲሰጡ ለማድረግ ፖሊስ በጋዜጠኞች እና በተቃዋሚዎች ላይ በደሎችን ይፈጽማል።

Ethiopia
(ናይሮቢ፣ ጥቅምት 7 ቀን 2006 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ባለስልጣናት አዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ዋና የማሰሪያና የምርመራ ጣቢያ ውስጥ በፖለቲካ ሳቢያ የተያዙ እስረኞችን እንደሚያሰቃዩ እና ለጎጂ አያያዝ እንደሚያጋለጡ ሂዩማን ራይትስ ዎች ዛሬ ይፋ ባደረገው ሪፖርት አስታወቀ፡፡ ማዕከላዊ በመባል በሚታወቀው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የሚፈጸሙ ህገ ወጥ ተግባራትን ለማስቆም እንዲሁም የሚፈጸሙትን በደሎች በተመለከተ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በገለልተኛ ወገን እንዲመረመሩ እና አጥፊዎቹንም ተጠያቂ ለማድረግ የኢትዮጵያ መንግስት አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ አለበት፡፡

ጠ/ሚኒስትሩ ተቃዋሚዎችን “ይሄ መንግስት ፈርቷል እያላችሁ ራሳችሁን አታሞኙ” አሉ


ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚ ሀይለማርያም ዛሬ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ መንግስት የጎዳና ላይ ነውጥ ከሚያሰቡት ሀይሎች ጋር ለመነጋገር የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።Thumbnail
አቶ ሀይለማርያም በተቃዋሚዎች በኩል የሚቀርበው ቅጥ ያጣ ፍረጃ እና የጥላቻ ፖለቲካ እንዲቆም  እንዲሁም የጎዳና ላይ ነውጥ እናደርጋለን በማለት የሚያስቡ ሀይሎችም ሀሳባቸውን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል። “የጎዳና ላይ ነውጥ ለማስነሳት በቂ መረጃ አለን ስንል “መንግስት ፈርቶ ማስፈራራት ጀመረ” እንባላለን ያሉት አቶ

Wednesday, October 16, 2013

የህወሓትን ፀረ ኢትዮጵያ አካሄድና ዓላማ በመቃወም የሕይወት መስዋእትነት የከፈሉ አመራር ነበሩ ወይ? ከነበሩስ እነማን ናቸው?


ከዚህ ቀጥለን የምንመለከተው ትኩረት ያልተሰጠውን ተሸፍኖ የነበረውን እና የህወሓት መሪዎች፣ በሕይወት ያሉትም የሞቱትም፣ ከወያኔ የተባረሩ አመራርም ጉዳዩ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ተዳፍኖ እንዲቀር ከባድ ጥረት እያደረጉበት ያለውን ነው።

በህወሓት የተፈጸመው እውንተኛ ታሪክና አሰቃቂ ወንጀሎች፣ የህወሓት አመራር በኢትዮጵያ ሃገራችን አሁንም  እየፈፀሙት የሚገኘው ግፍ በግልጽ ተጽፎ የወያኔ ጥቁር ታሪክ ለሕዝብ የሚቀርብበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። አሁንም እየቀረበ ነው።
ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) ለትግል የተሰማራው በየካቲት 11 ቀን 1967 ደደቢት በረሃ እንደመሸገ  ማሀብር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገብት) የተዘጋጀው ፕሮግራም የተረከበው ተሓህት ወይም የዛሬው ስሙ ሀወሓት ነው።

አለማቀፍ ጠበቆች የኢትዮጵያን ባለስልጣናት ለፍርድ ለማቅረብ እንቅስቃሴ ጀመሩ


በወጣት አብዱላሂ ሁሴን አማካኝነት በኢትዮጵያ የኦጋዴን ክፍል የተፈጸመውን የጦር ወንጀልና የሰብአዊ መብት ጥሰት ፊልም የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም በስዊድን ቁጥር አንድ ቴሌቪዥን በትናንትናው እለት መቅረቡን ተከትሎ አለማቀፉ ጠበቆች ጉዳዩን ወደ አለማቀፍ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እንቅስቃሴ ጀመረዋል።
ወጣት አብዱላሂ ለኢሳት እንደገለጸው ፊልሙ ከተላለፈ በሁዋላ ሚዲያዎች ሸፊ ሽፋን የሰጡት ሲሆን፣ ስቴላም የተባሉ የ አይ ሲ ጄ ጠበቃ ጉዳዩን ፍርድ ቤት እንደሚያቀርብ በሬዲዮ ይፋ አድርገዋል።

ለአፍሪካ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች ፍትሕ አይቀሬ ናት



ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ
ማስታወሻ ለአንባቢው፡፡ ባለፈው ሳምንት ሐተታዬ ‹‹የዘር አደን›› በሚል አሉባልታዊ ክስ  የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በተሰነዘረበት ክስ ደግፌው ተሟግቼለታለሁ፡፡ በዚህም ሳምንት ድጋፌን በመቀጠል እነዚህ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች የፈጠሙትን ግፍና በደል ጭቆና በመዘርዘር ራሳቸውን ነጻ በማድረግ የአይ ሲ ሲን (የኣለም ወንጀለኛ ፍርድ ቤት) ስም በማብጠልጠልና የቆመለትን ዓላማ የሳተ በማስመሰል ገዢዎችና አስፈጻሚዎ ቡችሎቻቸው ያነሱዋቸውን ማስረጃ ቢስ ውንጀላዎች በተጨባጭ ማስረጃ ድርጊቶታቸውንና ሸፍጣቸውን ይፋ ለማድረግ ወስኛለሁ፡፡ የኦክቶበር 11-12, 2013 የአፍሪካ አንድነት ‹‹መሪዎች›› የጨረባ ስብሰባ የተጠራውም ቴአትራዊ የልብ ወለድ ሴራ ለማካሄድና ነጻ ለመምሰል የሚያስችላቸውን ቅጥፈት ለማናፈስ ነው፡፡
በኔ እምነት አይ ሲ ሲ የዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ሕግጋት ትክክለኛውና ጠንካራው ምልክት ነው፡፡ አይ ሲ ሲ ላለፉት ጥቂት ዓመታት ስራውን በማከናወን ላይ ነው፡፡እስካሁን ያስመዘገባቸው ውጤቶች ጥቂት ቢሆኑም ለወደፊቱ ግን ያሻቸውን በደልና ግፍ ፈጥመው ግድያና አስገድዶ መድፈርን ሰብአዊ መብት በደልን አዘው በማስፈጸም በሥልጣናቸውም አላግባብ ባልገውና ተጠቅመው፤ ሃገርን አራዉተው፤ ሕዝብን በበደልና ግፍ ጫና አጉብጠውና አንበርክከው፤ በነጻ ሲቀመጡና ሲንደላቀቁ የነበሩትን እያጋለጠ ለፍርድ ለማቅረብ የሚችል ጠንካራ ተቋም እንደሚሆን እምነቴ ነው፡፡  የአፍሪካ ጨቋኝና የግፍ በደል ባለቤት የሆኑት ገዢዎች በሕዝቡ ላይ ሊኩራሩና ሊደነፉ፤ የሕግ የበላይነትን በመጨፍለቅ ሊቀጥሉ ይጥሩ ይሆናል፤ አሁን ግን አይ ሲ ሲ ስለመጣባቸውና ለሕዝቡ ወግኖ ስለቆመ ስሙ በተጠራ ጊዜ እየተርበደበዱና መግቢያ እያጡ በመሄዳቸው የአይ ሲ ሲን ስም በማጉደፍ ነጻ ለመሆን ቢጥሩ መንገድ ሁሉ፤ በደላቸው ሁሉ፤ ግፋቸው ሁሉ አይ ሲ ሲን እየቀሰቀሰባቸው በመሆኑ ኦክቶበር 13 2013 የቁም ተዝካራቸው ማውጫ አድርገው ሊሰባሰቡ ነው፡፡

‹‹ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መሞታቸው ተነግሮናል›› – (አቶ ስብሃት ነጋ)


ከዳዊት ሰለሞን
በኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት ወቅት ያበሩት የነበረው የጦር አውሮፕላን ተከስክሶና ቆስለው በሻዕብያ እጅ ለሁለተኛ ጊዜ የወደቁት ጀግናው ኢትዮጵያዊ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኤርትራ እስር ቤቶች በስቃይ ቆይተዋል፡፡
ጦርነቱ አብቅቶ ሁለቱ አገሮች የጦር ምርኮኞቻቸውን ሲቀያየሩ የኢትዮጵያ መንግስት በኮሎኔሉ ጉዳይ ገፍቶ መሄድ ባለመቻሉ በዛብህ ወደ አገራቸው ሳይመለሱ በኤርትራ እስር ቤት መቅረታቸውን የመንግስት ተቃዋሚዎች ይናገራሉ፡፡

የአስተዳደሩ ምርመራና ክስ ኤክስፐርት በቁጥጥር ሥር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ


-በቦሌ ጉምሩክ ኃላፊና በአንድ ባለሀብት ላይ የተዘጋጀው ክስ ሳይነበብ ቀረ

በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈጸሙት በሥልጣን ያላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው፣ በማረሚያ ቤት በሚገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት

Tuesday, October 15, 2013

ከ52 የአፍሪቃ ሃገራት መሪዎች በመልካም አስተዳደር ለተመረጡ የአፍሪቃ መሪዎች ለሚሰጠው ሽልማት በዚህ ዓመት መስፈርቱን ያሟላ መሪ አለማግኘቱን አስታወቀ


በመልካም አስተዳደር ለተመረጡ የአፍሪቃ መሪዎች ለሚሰጠው የሞኢ ኢብራሂም ሽልማት በዚህ ዓመት ተሸላሚ እንዳልተገኘ ድርጅቱ ዛሬ ለንደን ውስጥ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ።
8u7
ሞኢ ኢብራሂም የተባለው ድርጅት በመልካም አስተዳደር ለተመረጡ የአፍሪቃ መሪዎች ለሚሰጠው ሽልማት በዚህ ዓመት መስፈርቱን ያሟላ መሪ አለማግኘቱን አስታወቀ ። ድርጅቱ ዛሬ ለንደን ውስጥ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በዚህ ዓመት ተሸላሚ እንደሌለ አስታውቋል ። ከ52 የአፍሪቃ ሃገራት መሪዎች መካከል የድርጅቱን መስፈርት ያሟላ መሪ አለመገኘቱ በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አነጋጋሪ ጉዳይ ነበር ። ድርጅቱ ለአፍሪቃ ሃገራት የሰጠው የመልካም አስተዳደር ደረጃም ዛሬ ይፋ ሆኗል ።

አቶ አዲሱ ለገሰ አራት ምክትሎች ተመደቡላቸው


inauguration5

ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሕአዴግ ካድሬዎችን ለማሰልጠን የተገነባውን የፖለቲካ ማሠልጠኛ ተቋም በሚኒስትር ማዕረግ ሲመሩ የነበሩት አቶ አዲሱ ለገሰ ከኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የተውጣጡ ምክትሎች ተሹመውላቸዋል፡ ፡ ከብአዴን አቶ ለገሰ ቱሉ፣ ከደሕዴን አቶ ወንድሙ ገዛኸኝ፣ ከሕወሓት አቶ ነጋ በርሄ ሲሆኑ፣ ከኦሕዴድ የተወከለው አመራር እስካሁን አለመታወቁን ሪፖርተር ዘግቧል።

Monday, October 14, 2013

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰልፍ ክልከላ ቀጭን መስመር



ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መስከረም 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ለሁለተኛ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በበርካታ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ገለጻ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰልፍ የማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብት ዙሪያ የሰጡት ምላሽ ግን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ኤልሳቤጥ እቁባይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረበችው ጥያቄ የሚከተለው ነበር፡- ‹‹የትግል እንቅስቃሴአቸውን አገር ውስጥ እያደረጉ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ጊዜዎች በተለያዩ ከተማዎች ከመንግሥት ምላሽ ይፈልጋሉ ባሏቸው ጉዳዮች ላይ ሰላማዊ ሰልፎችን አድርገዋል፡፡ ምንም እንኳን ሰልፎቹን አስመልክቶ በመንግሥት ኮሚኒኬሽን በኩል የተሰጡ መግለጫዎች ቢኖሩም ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከቀረቡ ጥያቄዎች ‹ምላሽ ያሻቸዋል፣ አግባብነት አላቸው› ብለው መንግስትም በተለያየ መንገድ ከሚሰበስባቸው መረጃዎች የወሰዷቸው ጥያቄዎች አሉ ወይ››

ስንቱን አጣን! (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)



እንደኢትዮጵያ ባለ ኋላቀር አገር አገር ውስጥ መሠልጠን ብዙ ችግር አለበት፤ እኔ ራሴ በኮምፒዩተር መጻፍ ከጀመርሁ ሠላሳ ዓመት ሊሆነኝ ነው፤ ታዲያ መብራት ጠፋና የምሠራው ባጣ የቆዩ ወረቀቶችን ሳገላብጥ አንድ እአአ በዲሴምበር 26 1965 ከዱሮ ተማሪዬ የተጻፈልኝን ደብዳቤ አገኘሁ፤ በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በነበረ ከአንድ በጣም ጎበዝ ወጣት የተላከልኝ ነበረ፤ ከተመረቀ በኋላ በአንድ ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ ለጥቂት ዓመታት ሠርቶ ትምህርቱን ለመቀጠል ወደአሜሪካ ሄዶ በሎዝ አንጄለስ አካባቢ ከሚገኝ ትምህርት ቤት ገብቶ ነበር፤ ደብዳቤውን የጻፈልኝ ከዚያ ነው፤ ደብዳቤው ሰባት ገጾች አሉት፤ ከሰባቱ ገጾች አምስቱ ስለኢትዮጵያ ያለውን ስጋት የሚገልጽ ነው፤ በሎዝ አንጀለስ አካባቢ ካሉ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት በሚያደርግበት ጊዜ ሁሉ ብዙዎቹ የሚያሳዩት የመንደረኛነት ስሜት እያበሳጨው የተማሩት ሰዎች በእንደዚህ ያለ ማኅበረሰባዊ ኋላቀርነት ውስጥ ሆነው ኢትዮጵያ የምትባለው አገር እንዴት መራመድ ትችላለች? እያለ ይሰጋ ነበር።

Sunday, October 13, 2013

የፖለቲካ ፓርቲዎች ሥር ነቀል የአስተሳሰብና የአቋም ለውጥ አስፈላጊነት


ከእንጉዳይ በቀለ፣ አዲስ አበባ ሕወሐት/ኢህአዴግ ኢትዮጵያን በጉልበትና በግፍ መግዛት ከጀመረ 22ኛ ዓመቱን ይዟል፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ እንደ ሟርትአይታይብኝና ይህ ቁጥር አሁን ካለው እውነታ በመነሣት ወደ ሠላሳና አርባ ብሎም ሃምሳ የማይዘልቅበት ምንም ምክንያት ያለ አይመስልም.. ይህን ለመገመት ውስብስብ ስሌት ወይንም የሂሣብ ቀመር አይጠይቅም፡፡ በአገር ቤት ያለውን አያያዝና በተቃዋሚዎች በኩል ያለውን እንቅስቃሴ በመቃኘት ስህተት ነው ሊባል ከማይችል ድምዳሜ ላይ ሊደረስ ይቻላል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአገራችን ፖለቲካ በእጅጉ ከመሰላቸቱ የተነሣ መፃዒ ዕድል ፈንታውን ከእግዚአብሔር እንጂ ከተቃዋሚዎች ወይንም ከፖለቲካ ድርጅቶች ተስፋ ማድረግ ከተወ ሰነባብቷል፡፡ አንደኛው ምክንያቱም ተስፋ ሊጥልበት

ETV በቦሌ አዲስ አበባ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን ዘገበ


ዘገባው የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የተቀነባበረ ይሁን አይሁን በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠ የETV ዘገባ እንደወረደ አቅርቤዋለው
እሁድ 3 2006 ዓም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የቤት ቁጥር 2333 ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ሁለት ግለሰቦች ተከራይተው በሚኖሩበት ቤት ውስጥ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ ጸረ ሽብር ሀይል ገለጸ፡፡
በፈንጂ ፍንዳታው ሁለቱ ግለሰቦች ህይወታቸው አልፏል፡፡

መሐሙድ አህመድ የቴዲ አፍሮን ኮንሰርት አቋርጦ ሄደ


የኢትዮጵያውያን በመላው አለም መበተን ለአርቲስቶቻችን በተለይም በሙዚቃው ኢንዳስትሪ ለተሰማሩ ጥሩ የገቢ ምንጭ እየሆነላቸው ይገኛል፡፡ አቀንቃኞቻችን በውጪ የሚገኙ ዳያስፖራዎቻችንን ለማዝናናት፣ የአገር ቤት ፍቅራቸውን የሚቀሰቅሱና ስሜት የሚኮረኩሩ ዘፈኖችን በሙዚቃ አልበሞቻቸው በማካተት በአውሮፓ፣ በአውስትራሊያ፣ በመካከለኛው ምስራቅና በአሜሪካ በወኪሎች አማካኝነት ኮንሰርቶችን በማዘጋጀት ኪሳቸውን አደልበው ወደ አገር ቤት ይመለሳሉ፣ አንዳንዶቹም ዶላሩ ጥሟቸው በወጡበት ቀርተው ኑሯቸውን ይመሰርታሉ፡፡

Saturday, October 12, 2013

የኢህአዲግ አፈና በሰማያዊ አመራሮች እና አባላት ላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!!


የኢህአዲግ አፈና በሰማያዊ አመራሮች እና አባላት ላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!!
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ዉስጥ ለሰማያዊ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ተከራይቶ የነበረዉን ቤት ከዛሬ ጥቅምት 1 2006 ጀምሮ ለመጠቀም

“የይሉኝታ ፖለቲካ ይገድላል”


mitmitta1

“ሙሉ ኢትዮጵያዊ ነኝ” ትላለች። የተወለደችው ዱከም ነው። በቀድሞው አጠራር በኢትዮጵያ የተለያዩ ጠቅላይ ግዛቶች ኖራለች። ሐረር፣ ባህርዳር፣ አስመራ፣ አዲስ አበባን በመጥቀስ ልዩ ትዝታዎች እንዳሏት ትናገራለች። ከዛሬ ሃያ ዓመት በፊት አሜሪካ ከትማለች።

የቢቢኤኑ ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ በአሜሪካ የሚገኙትን አቶ ስብሃት ነጋን አፋጠጣቸው ድምፃችን ይሰማ በማለ


የቢቢኤኑ ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ በአሜሪካ የሚገኙትን አቶ ስብሃት ነጋን አፋጠጣቸው ድምፃችን ይሰማ በማለት ድምፁን አስምትዋል
Breaking News ! Ato Sebhat Neggaa begazetegna Sadiq Ahmed Washington DC lai begeff Qalitina Qillenttoo Seletaserut wendemochachen gudai bettyaqee afatetew.
For More see this video

እስክንድር ነጋ በአራት ጎብኚዎች ብቻ እንዲጎበኝ ተደረገ


1394241_527514827333456_269824761_n
ታዋቂው የፖለቲካ ተንታኝና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በሚገኝበት የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር በተላለፈ ትዕዛዝ መሰረት የጎብኚዎቹ ቅጥር መወሰኑን የማረሚያ ቤቱ ምንጮች ለፍኖተ ነጻነት ገለጹ፡፡ የመስከረም 19/2006 ሰላማዊ ሰልፍ ብስጭት ከፈጠረባቸው አካላት መካከል አንዱ የሆነው የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ብስጭቱን አደባባይ ያወጡበትን እርምጃዎች መውሰድ መጀመሩ እያነጋገረ ነው፡፡ለአንዷለም አራጌ የጎብኚዎቹን ስም እንዲሰጥ ካልሆነ ግን በማንም እንደማይጎበኝ የነገረው አስተዳደሩ የእስክንድርን ጠያቂዎች ቁጥር በአራት መወሰኑ ታውቋል፡፡