Monday, April 28, 2014

ሠማያዊ ፓርቲ የነፃነት ትግልና የሃበሻ ጀብዱ

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

በቅርቡ የሴቶችን ቀን አስመልክቶ በተደረገ የሩጫ ዝግጅት ወቅት የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆችነ ነን ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች “አትለያዩን! አትከፋፍሉን! ነፃነት እንሻለን! ለድሃው ይታሰብለት! ኑሮ ከበደን! ውሃ ጠማን! መብራት ናፈቀን!” በማለት በጣም ሰብዓዊና እናታዊ ጥሪ ጮክ ብለው አሰምተው ነበር። ይህም መልካም ድርጊታቸው ለፍትህና ለአንድነት የሚደረግ ህዝባዊ ጥሪ በሚያስበርግጋቸው የወያኔ ባለስልጣናት ሁከት ፈጠራ ተብሎ ተወነጀሉ። ፕሮፌሰር አልማርያም በተቆጣው ብዕራቸው

… ያገሬ ወይዛዝርቶች በምህረት አልባ ጨካኞች ሲንገላቱና ሲወገሩ ከዳር ቆሜ ማየትን ህሊናዬ ፈጽሞ አይፈቅድልኝም። ይልቁንም የእንግልታቸው ምክንያት ሰብዓዊ በሆነው መብታቸው ድምፃቸውን ስላሰሙ በመሆኑ የነሱና የመሰሎቻቸውን ጥሪ በዚህም ሳቢያ የሚደርስባቸውን አበሳ ሁሉ ለአለም አሳውቅ ዘንድ ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ…

ብለው ነበር። ከርሳቸው ድምጽ ጋር በማበር የሚያስተጋቡ ድምጾች ይኖሩ ዘንድ እውነት ነውና የኔንም ድርሻ እነሆ እጮሃለሁ።

Addis Ababa Semayawi (Blue) Party Rally [video]


Semayawi Party (Blue Party) Ethiopia’s most active opposition party held rare protest against the ruling regime TPLF/EPRDF on April 27, 2014 in the capital Addis Ababa.

Ethiopia arrests journalists, bloggers

NAIROBI, Kenya — Rights groups are calling on Ethiopia’s government to release six bloggers and three journalists arrested last week.
Human Rights Watch on Monday called on U.S. Secretary of State John Kerry, who visits Ethiopia on Tuesday, to urge Ethiopian officials to release the nine.

Sunday, April 27, 2014

Live Update: Semayawi Party Protest Rally, April 27, 2014

ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም… እየተዘፈነ ይገኛል።

ከሚደመጡ መፈክሮች መካከል….
ተርበናል፣ ተጠምተናል፣ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ማሟላት አልቻልንም!
semayawi protest live addis ababa
——————————————————–

—————————

Saturday, April 26, 2014

Six members of Zone Nine, group of bloggers and activists are arrested today late in the afternoon at 5:20 pm by Ethiopian security forces.
Zone 9 bloggers are arrested in Ethiopia Team members Befeqadu Hailu, Atnaf Berahane, Mahlet Fantahun, Zelalem Kiberet, Natnael Feleke and Abel Wabela are all under custody on arrest warrant.

Thursday, April 24, 2014

"ሱሪህን አውልቅ" አለኝ። "እኔ ወንድ ነኝ፡፡ ወንድ ፊት ሱሪዬን አላወልቅም። ወንድ የወንድን ገላ ለማየት አይጓጓም፡፡

....ወድያው ከፀሀይ መሞቅ እንደገባሁ 49 ቁጥር ቢሮ ለምርመራ ተጠራሁ፤ በካቴና ታስሬ ነበር የመጣሁት። አለማየሁ፣ "መርማሪ ይለወጥልኝ ትላለህ አለ? ምን አይነት መርማሪ ነው የምትፈገው?" አለኝ። ዝም አልኩት።
"ሱሪህን አውልቅ" አለኝ።
"እኔ ወንድ ነኝ፡፡ ወንድ ፊት ሱሪዬን አላወልቅም። ወንድ የወንድን ገላ ለማየት አይጓጓም፡፡ ሱሪዬን አላወልቅም። ከፈለግክ አውልቀው" ስለው ደህንነቱ ተናዶ ምራቁን ተፍቶብኝ በቦክስ ሆዴን አለው። የሥነ ልቦና ጫና ስለደረኩበት ሱሪዬን ሳያወልቅ ቀረ። ኢንስፔክተር ዓለማየሁ ተቀብሎ ፂሜን ሲነጭ አስጮኸኝ። "ዝም በል!" ብሎ ጉሮሮዬን ሲያንቀኝ ትንፋሽ አጥሮኝ ዝም አልኩ። ፊት ለፊት ታስሮ የነበረውን ካቴና ፈትቶ ወደኋላ አሰረኝ። ደህንነቱ ቀድሞ ፂሜን እየነጨ በስክሪብቶ ጫፍ ጠቀጠቀኝ።

AN URGENT APPEAL – From Mesfin Wolde-Mariam


The UN Human Rights Commission
The African Union Human Rights Commission
The International Red Cross
Amnesty International
Human Rights Watch
And
All Men and Women of GOOD WILL
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist. There are not many Ethiopians of her caliber inside the country. She has been languishing in the famous Ethiopian Prison in Qalliti for almost three years. She was charged of terrorism, a crime she totally abhors. She was sentenced first for eighteen years but later reduced to three.

Thursday, April 17, 2014

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት ከስልጣን የምነሳ ከሆነ ክልሉ የራሱን እድል በራሱ ይወስናል አሉ


ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ ምክር ቤት በሶማሊ ክልል የሚፈጸመው ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት በክልሉ ያሉትን ባለስልጣኖች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የኢህአዴግን ባለስልጣኖችን በአለማቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት የሚያስጠይቅ መሆኑን ድምዳሜ ላይ የደረሰው ኢህአዴግ፣ ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሃመድ ኡመርን ለማውረድ እንቅስቃሴ መጀመሩ ፕሬዚዳንቱ ይህንን ንግግር እንዲናገሩ እንዳደረጋቸው ምንጮች ገልጸዋል።