Monday, August 19, 2013

ታሎው ኦይል የተባለው ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያውን የነዳጅ ክምችት ማውጣት እንደሚችል ገለጸ


http://api.ning.com/files/uHRAM*dGlS-LmWsm337OZ6BEglttsbvpfPbxSHGm9FJDkyr-usatxf1PiO0iM-XNfEPd*2amUqb2oyvjr4yhddifHjfSxocZ/sabisa.jpg
የኬንያን የነዳጅ ክምችት ያገኘው የእንግሊዙ ታሎው ኦይል እንደገለጸው የነዳጅ ክምችቱ ወደ ጎረቤት ሀገር አትዮጵያ ሊቀጥል ይችላል የሚል እሳቤ ላይ እንዳለ ዋሰሽንግተን ፖስት ዘገበ፡፡ በዚህም መሰረት ታሎው ኦይል ፣ አፍሪካ ኦይል ኮርፖሬሽንና ማራቶን ኦይል ኮርፖሬሽን በደቡብ ኦሞ አካባቢ የሳቢሳ ፕሮጄክት ጉድጓዶችን እንደሚያጠናቅቁ ተገለጸ፡፡
ማርቲን ሙቦጎ የተባለ በኬንያ የታሎው ኦይል ማኔጀር እንዳለው “ የመጀመሪያው የነዳጅ ግኝት በኢትዮጵያ ትልቅ ይሆናል ለሀገሪቱም ትልቅ ታሪክ ነው ፡፡’’ ብሏል
ታሎው ኦይል ባሁኑ ሰዓት የምስራቅ አፍሪካን ተራራማ ቦታዎች በመቃኘት ላይ ሲሆን እይታው በኡጋንዳና በኬንያ የነዳጅ በረከት አስገኝቶለታል፡፡ ለድርጅቱ አዲስ የነዳጅ ክምችት በኢትዮጵያ ተገኘ ማለት አዲስ የነዳጅ ግዛት ሲሆን ለሀገሪቱ መንግስት ደግሞ ከውጭ የሚገዛው የሀይል ምንጭ ቀርቶ እንዲሁም አብዛኛው ኢኮኖሚ ከቡና ሽያጭ ቀረጥ ከማግኘት ይልቅ በነዳጅ ዘይት የተደገፈ ኢኮኖሚ እንዲኖረው ያደርጋል፡፡

Saturday, August 17, 2013

ጁነዲን ሳዶ በወያኔ ተገደሉ ሲል ayyaantuu.com ዘገበ

junedinJunedin Sado, an Ethiopian politician and former governor of the state of Oromia was killed by Woyyanee under cover agents in Robbii, Shewawhen he secretly returned to the country from Kenya.

He was thrown out of the EPRDF government due to his disagreement with certain policies that the ruling government imposed on the governing system and alleged accusation of involvement in his wife, Habibe Muhammad’s plot of terrorism in the country.

Thursday, August 15, 2013

የሃዘን እንጉርጉሮ … ለግብፅ


2013814143731829665_8የሃዘን እንጉርጉሮ … ለግብፅ
ግብጽ ሆይ እንዴት አለሽ አልልሽም ከቶ… ነገርሽን እያየሁ ዜና ላይ ተሰጥቶ… እኔ ልሰጣልሽ ብዬም ባልልሽ… ሀዘንሽን አዘንኩት ተሰማኝ ልቅሶሽ… እሳት ሲቀጣጠል ሰው ሲጠበስ ለጉድ… ግንቡ ቤተ አምልኮሽ ሲቀየር ወደ አመድ…
ምን ርግማን ይሆን ምንስ ያገር ጣጣ… በሌሎች ሲፈራ ዛሬ ባንቺ መጣ፤
ያኔ…
እኛ በወር እቁብ እንኳን መጣል ሲቸግረን፤ በአስራ ስምት ቀናት አምባ ገነን ጥለሽ እንዳላስቀናሽን፣ ከዛም በድጋሚ ጥቂትም ሳትቆዬ ህዝብሽ ግራ እና ቀኝ ሁለት ወገን ተሰልፎ… አንዱ ወታደሩን አንዱ ህጉን አቅፎ ግልበጣ አይሉት ልወጣ ግራ የሚያጋባ በእውኑ፣ ፕረዘዳንት ሲወርድ እንደዋዛ ከዙፋኑ፣ “የማናት ቀልባጣ የማን ተሸቀርቃሪ እንደ አልባሶቿ ምትለዋውጥ መሪ” ብለን ስንደነቅ በሰራሽው ስራ፤ እሱን ተከተሎ መጣብሽ መከራ…

Friday, August 9, 2013

በመንግሰት የችግር አፈታት ዘዴዎች ዛሬም አዝነናል፧ አፍረናልም!!!!

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

ከሁሉም በማሰቀደም ሰማያዊ ፓርቲ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳቹ፣ በዓሉ የሰላምና የደሰታ እንዲሆንላቹ ኢድ ሙባረክ በማለት ምኞቱን ይገልፃል ::Blue Party Ethiopia
ኢሕአደግ መራሹ መንግሰት ተቋማትን የመቆጣጠር አባዜው ከግዜ ወደ ግዜ እየባሰባት በመምጣቱ ዛሬም እጁን ያላሰገባበት ምንም አይነት ተቋምና አሰተሳሰብ ባይኖርም በተለይ ባለፈው አንድ አመት ተኩል ጀምሮ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር በፈጣረው እሰጥ አገባ መፍትሔ አጥቶ እሰከ አሁኗ ሰአት ቀጥሏል:: ሰማያዊ ታርቲ የመንግሰትን በሐይማኖት ጣልቃ መግባት አጥብቆ በመቃወም የራሳቸውን የእሰልምና እምነት መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን እንዲፈታና ችግሩም በውይይት እንዲፈታ በተደጋጋሚ ግዜ ጥሪውን አቅርቧል::
ነገር ግን መንግሰ ችግሮችን በሐይል ጨፍልቄ እፈታለሁ የሚል የተለመደ አካሔድ ለፓርቲያችን ጥሪ የሰጠው ምላሽ ካለመኖሩም በላይ የፓርቲያችንን ሰም በማጉደፍ የሀገር ጠላትና አሸባሪ ፓርቲ አድርጎ ለማሳየት ጎምበስ ቀና በማለት ላይ ይገኛል::

Thursday, August 8, 2013

Amnesty International: Ethiopian repression of Muslim protests must stop


Amnesty International on Ethiopian Muslims
Young Ethiopian Muslim girl, attacked by Ethiopian government forces during Eid al-Fitr celebrations in Addis Ababa. August 08, 2013
The Ethiopian government must end its use of repressive tactics against demonstrators, following initial reports of widespread arrests of Muslim protestors during this morning’s Eid al-Fitr celebrations, said Amnesty International today.

ታማኝ በየነ እና ቴዲ አፍሮ ከአመታት በኋላ መድረክ ላይ ተገናኙ


“ጥቁር ሰው” በድጋሚ ሲዘፈን ሌላ የሚያስጮህ ነገር እንደሚመጣ ያልጠበቀው የአውሮፓ ታዳሚ፤ ጉሮሮው እስኪነቃ እንደገና ጮኸ። ታዳሚው ከፊት ወንበር ላይ በVIP ላይ ታማኝ በየነ መቀመጡንም ሆነ፤ በስፍራው መገኘቱን አያውቅም። ቴዲ አፍሮም “ጥቁር ሰው”ን እንደገና ከማቀንቀን ውጪ፤ የድሮ ጓደኛው ወደ መድረክ ይመጣል ብሎ አልጠበቀም። የሆነው ግን እንዲህ ሆነ።
ሁለቱም ኢትዮጵያ ያፈራቻቸው የዘመኑ እውቅ አርቲስቶች ናቸው – ታማኝ በየነ እና ቴዲ አፍሮ።

ሰበር ዜና! የፌደራል ፕሊስ እርምጃ እየወሰደ ነው!




ድምፃችን ይሰማ
እስከ አሁን ባለው መረጃ በአዲስ አበባ፣ በወልቂጤ፣ በደሴ፣ በአዳማ፣…የመንግስት ታጣቂዎች የዒድ ክብረ በዓልን ለመፈጸም የወጡ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ኃይል የተቀላቀለበት ድብደባ ፈጽመዋል፡፡ መንግስት ለኢትዮጵያውያን ሙስሊም ዜጎቹ ያለውን ከልክ ያለፈ ጥላቻ በዛሬውም በኢድ በዓል ቀን አሳይቷል፡፡
Ethiopian Muslims

ወያኔ እንደ ቆሰለ አውሬ…




Author and writer Tesfaye Zenebe from Norway
ከተስፋዬ ዘነበ (ኖርዌይ በርገን)
ዘመንኑ ያለቀበት ስርዓት፣ መዋቅሩ የፈረሰ ስርዓት፣ ሁለመናው እኩይ በሆነ በሕዝብና ሃገር ጥላቻ የተተበተበ ስርዓት፣ የእድሜ ዘመኑ እያለቀና የማስተዳደርና የመምራት አቅም ማጣት ሲጀምር ለስልጣኑና በስልጣን ዘመኑ የመዘበረውን የሕዝብና የሃገር ሃብት ለማስጠበቅ የውር ድንብሩን ዪዳክራል፡፡
ይህው በመቃብር አፋፍ ላይ ያለው የወያኔ ዘረኛ ቡድን ላለፉት ሁለት አስርተ አመታት በሕዝብና በሃገር ላይ ሲያደርስ የነበረውን  እጅግ ዘግናኝ ክህደት ከማንም ኢትዮጲያዊ አህምሮ የሚፋቅ ባይሆንም ስርዓቱ ቤሔራዊ ስሜት(ሃገራዊ ስሜት) በማጣቱ ምክኒያት የሚያደርሰውን ዘርፈ ብዙ ችግር የተቃወሙ ንፁሃን ዜጎች ወይም እንደ ዜጋ በሃገራቸው ውስጥ በሰላም የመኖር ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በግፈኞች ተነጥቀው ነፃነታቸውን ለማስመለስ ፍትህ የጠየቁ ሁሉ በአሸባሪው ስርዓት አሸባሪ ተብለው ሲፈረጁ መመልከት የተለመደ ድራማ ነው፡፡

በባንዲራ ያሸበረቀው አገር አቀፉ የዒድ ክብረ በዓል እና ተቃውሞ እጅግ አስራሚ ድባብ ፈጥሯል




ድምፃችን ይሰማ
የዛሬው ተቃውሞ በፅሁፍና በፎቶ በከፊል!
ከማለዳው 1፡20
በአዲስ አበባ ስታዲየም በሁሉም አቅጣጫ ያለን ሙስሊሞች ከፍተኛ ጥንቃቄ እናድረግ፡፡ በአካባቢያችንን ያሉ ኹኔታዎችን በደምብ እየቃኘን፡፡
ከማለዳው 1፡27
በባንዲራ ያሸበረቀው አገር አቀፉ የዒድ ክብረ በዓል እና ተቃውሞ እጅግ አስገራሚ ድባብ ፈጥሯል፡፡ ግና ምኑም አልተነካም፡፡ አልሀምዱሊላህ!
Ethiopian Muslims
ከማለዳው 1፡30
አዲስ አበባ ስታዲየም እየሞላ ነው፡፡ በጣም ጥቂት ቀርቶታል፡፡
ከማለዳው 1፡34
በጣም በርካታ ሙስሊሞች በመንገድ ላይ ተይዘዋል፡፡ መንግስት ሕገ መንግስታዊ መብታችንን በዚህ በበዓል ቀን እንኳ ለማክበር ፈቃደኛ አይደለም፡፡
ከማለዳው 1፡38

Tuesday, August 6, 2013

ለዜጎች የሚቆረቆሩ የመንግስት ተወካዮችን አፋልጉኝ!

ኮንትራቱስ ይቁም፣ የቀሩትን ዜጎች መብት ማን ያስከብር?

haile saudi


ሳውዲዎች ከኢትዮጵያ ከኬንያና ከኢንዶኖዥያ የቤት ሰራተኛ ቅጥር ካቆሙ ሰነባበተ! ይህነኑ ተከትሎ የቤት ሰራተኛ እጥረት የሳውዲዎች መነጋገሪያ ሆኗል። ባለጸጎቹ የሳውዲ ዜጎች በያዝነው የረመዳን ወር ብቻ 32 ቢሊዮን ሪያል የሚገመት ገንዘብ በሃገር ውስጥ ገበያ ልውውጥ ላይ እንደዋሉ በሰማን መባቻ የሳውዲዎች ችግር ሆኖ በመነገር ላይ ያለው የቤት የሰራተኛ አቅርቦቱን ጉዳይ ነው። ይህንንም የሃገሪቱ ታዋቂ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተው በመዘገብ ላይ ናቸው ።

ሰባር ዜና-አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ ከአገር ሸሽተው ጥገኝነት በመጠየቅ አሜሪካ ገቡ!

ድምፃችን ይሰማ
ማክሰኞ ሐምሌ 30/2005
‹‹ህሊናዬ የማያምንበትን እንድሰራ ተገድጃለሁ›› አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ
የመንግስት ክስ መጨረሻው በውል እንኳ አልታወቀም፤ ቀጠሮውም ም እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም!
የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን፣ አሊሞችንና ዳኢዎችን መንግስት በሀሰት በሽብር ወንጀል ጠርጠሮ ከከሰሳቸዉ አንድ አመት ቢያልፍም እስካሁን እልባት ላይ አለመደረሱ ይታወቃል፡፡ በዚህ ክስ ውስጥ ከከሳሽ መንግስት አቃቢያን ህግ መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ቴድሮስ ባህሩ ‹‹ህሊናየ የማያምንበትን እንድሰራ ተገድጃለሁ›› በማለት አገራቸውንና ስራቸዉን ጥለዉ ከአገር ሸሽተው ጥገኝነት በመጠየቅ አሜሪካ መግባታቸው ተረጋገጠ፡፡ አቃቤ ሕግ ቴዎድሮስ ባህሩ ሲሰሩ የነበረበትን የስራ ጉዳይ ሰነድ እንኳን ሳያስረክቡ ጥገኝነት ጠይቀዉ ከነቤተሰባቸዉ አሜሪካ እንደገቡ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

Sunday, August 4, 2013

ኮፈሌ በ ንጹሃን ደም ታጠበች! ቁጥሩ የበዛ ሰው ተገሏል

የ ኮፈሌ ወንድሞቻችን በ ወያኔ ቡችሎች ሲገደሉ ሲደበደቡና ሲታፈሱ ውለዋል፦ ምንም ላልታጠቁ ንጹሃን በ ታንክ የታገዘ 40 ኦራል ሰራዊት ቃታውን ሳበ። የሟቾች ቁጥርም 25ደርሷል :: 1500 ሰዎች ታስረዋል :: ሆስፒታሎች በ ቁስለኞች ሞልተዋል የ ሟቾች አስከሬን ከ መስጊዶች እንዳይወጣ ተከልክሏል ። ፌደራሎች ያገኙትን መኪና መስተዋት ይሰብራሉ። ETVም የተለመደ ድራማውን ሲሰራ ዋለ።

ህገ-መንግስታዊ መብታችንን ሳንገል እየሞትን እናስከብራለን! አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ሰኔ 13 ቀን 2005 ዓ.ም በጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቆ ወደ ንቅናቄው ከገባ ጊዜ ጀምሮ በርካታ ህዝባዊ ድጋፍና በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት እና የነፃነት ጥያቄ ድምፅ ከሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች በመደመጥ ላይ ይገኛል፡፡
በአንፃሩ ገዥው ፓርቲ የህዝቡን የነፃነት ድምፅ ለማፈን ንቅናቄያአችንን ከጀመርን እለት ጀምሮ በርካታ መሰናክሎችን እየፈፀመ ይገኛል፡፡

Saturday, August 3, 2013

ከአንድ ሺህ በላይ ሙስሊሞች ታፍሰው ታስረዋል

የወያኔ አገዛዝ በሰላማዊ መንገድ “መንግስት በሀይማኖታቸን ጣልቃ መግባቱን ያቁም” በማለት ከአንድ አመት በላይ ተቃውሞ እያሰሙ ባሉ ሙስሊሞች ላይ የሀይል እርምጃ እወስዳለው ብሎ መግለጫ ማውጣቱን ተከትሎ፣ የአንቅስቃሴው አስተባባሪዎች በመላ ሀገሪቱ ሊደረጉ ታቅደው የነበሩ ተቃውሞዎችን መሰረዛቸው ይታወቃል። ይሁንና አላማቸው ማሸበር እና ማሸማቀቅ የሆነው የወያኔ ታጣቂዎች በመላ ሀገሪቱ የተለመደ ሀይማኖታዊ ጸሎታቸውን ለማድረስ ወደየመስኪዶቹ ጎራ ያሉትን ሁሉ ሰብስበው አስረዋል። ቪኦኤ በዚህ ጉዳይ ላይ ዘገባ ይዟል።

Ethiopian Muslims protest, Addis Ababa

Friday, August 2, 2013

እንደራሴ ስሚዝ አዲስ አበባ ሊሄዱ ነው

http://www.goolgule.com/የኢህአዴግ መልስ በጉጉት ይጠበቃል

chris smith


አሜሪካና ሌሎች ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በሙሉ በ”አዲስ አበባው” አገዛዝ ላይ ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ያለ አንዳች ማወላወል ማሳየት እንደሚገባቸው አሳስበው የነበሩት ኮንግረንስ ማን ክሪስ ስሚዝና ባልደረባቸው እንደራሴ ኬረን ባስ አዲስ አበባ እንደሚገቡ ተጠቆመ። በሰኔ (ጁን) ወር “… የአሜሪካ መንግስትም ሆነ ሌሎች የምዕራብ አገራት፣ ኢህአዴግ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈጸመ ያለውን ተግባር በመረዳት አቋማቸውን በግልጽ ማስቀመጥ ይገባቸዋል” የሚል ጥሪ ያስተላለፉት ክሪስ ስሚዝ አዲስ አበባ መምጣት ኢህአዴግን እንዳሳሰበው ለማወቅ ተችሏል።

ድምፃችን ይሰማ፣ ለጁምአ ሐምሌ 26 የታቀዱ ተቃውሞዎች በመላው አገሪቱ አይኖሩም!

የመንግስት የሽብር መግለጫ የሕዝብን አሸናፊነት ያረጋገጠ ነው!

ጁምአ ሐምሌ 26/2005
ሁለት ዓመቱን ሊደፍን በጣም ጥቂት ወራት የቀሩት የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የመብት ማስከበር ሰላማዊ ንቅናቄ እጅግ አስገራሚ ምእራፎችን ተሻግሮ እዚህ ደርሷል፡፡ ንቅናቄው እንደአጀንዳ ያነሳቸው ተፈጥሯዊ እንዲሁም መሰረታዊ የህገ-መንግስት መብቶችና ደንጋጌዎችን መከበር ነው፡፡ ለተጠቀሱት ጊዜያት ያህል በሰላማዊና ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን በጠበቀ መልኩ ያለምንም እንከን የተደረጉት የተቃውሞ ትእይንቶች ብዙዎችን ግርምት ውስጥ ከመክተት በዘለለ መንግስት እውነት በራቀው አንደበቱ /ዜጎች ግብር በሚከፍሉባቸው መንግስታዊ ብዙሀን መገናኛዎች/ ንቅናቄውን ለማጠልሸት የሰነዘራቸው ስፍር ቀጥር የሌላቸው ውንጀላዎች መክነው እንዲቀሩ ዋነኛ ሚና ተጫውቷል፡፡

Thursday, August 1, 2013

ሽብርንና ‘ፀረሽብር ሕግ’ን አልደግፍም .! (በፀረሽብር ሕጉ ተሸብረን) የመናገር ነፃነታችንን አሳልፈን አልሰጠንም


የኢህአዴግ መንግስት በኢቲቪ በኩል ስለ ‘ሽብር’ና የ‘ፀረሽብር ሕግ’ አስፈላጊነት ያወራል። አንዳንድ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስለ ‘ፀረሽብር’ ሕጉ ኢ-ሕጋዊነት ይሰብካሉ።

እኔም የፀረሽብር ሕጉ ከማይደግፉ ሰዎች ጋር እንደምሰለፍ ካሳወቅኩ ከጥቂት ግዜ በኋላ አንድ የምወደው የህወሓት አባል የሆነ ጓደኛዬ እንዲህ ሲል በውስጥ መልእክት ላከብኝ፣

“ፀረሽብር ሕግ መቃወም ኮ ሽብርን መደገፍ ነው። አንዳንድ አክራሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ ስም ሽብርተኝነትን ማስፋፋት ይፈልጋሉ። ዓመፅ ቀስቅሰው እስላማዊ መንግስት ማቋቋም ይፈልጋሉ። በኢትዮዽያ ዓመፅ ተቀሰቀሰ ማለት ደሞ ልክ እንደ ሶርያ ቀውስ ነው የሚሆነው።”

ሽብር ምንድነው? ሽብር ‘ኮ ሃይል ተጠቅሞ ወይ ሃይል የመጥቀም ዛቻ በማሰማት ሌሎች ሰዎች ሰግተው፣ ፈርተው የግል ዓላማውን እንዲያሳኩለት ማድረግ መቻል ወይ እርምጃ መውሰድ ነው።

እኔ ሽብርን አልደግፍም። የኢህአዴግ መንግስት ከተቃወምነው አንዳንድ ችግሮች ሊያደርስብን እንደሚችል አውቃለሁ። በዚህ መሰረት የመንግስትን ቅጣት (እነሱ የማይፈልጉትን ከሰራን ማለት ነው) ፈርተን፣ ሰግተን ገዢውን ፓርቲ እንድንደግፍ ወይ ቢያንስ እንዳንቃወም ጥረት እናደርጋለን። ይህ የሚቃወሙትን ሰዎች በማግለል መቃወማቸውን እንዲያቆሙ የማድረግ ተግባር በራሱ ዜጎችን ማሸበር ነው። መንግስት ዜጎችን ያሸብራል፤ ሳይፈልጉ ግን ፈርተው እንዲገዙ ያደርጋል። ስለዚህ የኢህአዴግ ተግባር የሽብር ተግባር ነው። ሽብር አልደግፍም። የሽብር ተግባር እቃወማለሁ። ለዚህም ነው የኢህአዴግን መንግስት የምቃወመው።

በጦር ሀይሎች፤ጎጃምበረንዳ እና ሌሎች አካባቢዎች ሙስሊሞች በፖሊስ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተወረወሩ ነው፡፡

ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሙስሊሞች በፖሊስ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተወረወሩ ነው፡፡
በዛሬው እለት በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ቅጥራው በውል ያልታወቁ ሙስሊሞች በፖሊሶች እየታፈሱ እንደሆነ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
የረመዳንን ወር ተከትሎ ከፍተኛ ተቃውሞ በመደረጉ የተደናገጠው መንግስት የነገውን ተቃውሞ ለማኮላሸት በዛሬ ምሽት ብዛት ያላቸውን ወንድሞቻችን እያፈሰ ወደ እስር ቤት እያጎረ ይገኛል፡፡

የሥላሴዎች እርግማን፤ (አንድ) አዳክሞ ማደህየት

መስፍን ወልደ ማርያም

ፋክት መጽሔት
አዳክሞ ማደህየት የወያኔ ትልቅና ዋና መሣሪያ ሆኖ አገልግሎአል፤ ወያኔ ከኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አርባ ያህል መምህራንን ያስወጣው ገና በጠዋቱ ነበር፤ ከቴሌ ከመብራት ኃይልና ከባንክ ሰዎችን እየመነጠረ ያስወጣው በዘር አመካኝቶ ቢሆንም በትምህርታቸውና በልምዳቸው የጠጠሩበትን ሰዎች እንደሆነ ሁሉም የሚያውቀው ነው፤ እንደፐሮፌሰር ዓሥራት ያለውን በሁለት የታወቁ የእንግሊዝ ዩኒቨርሲቲዎች የተመሰከረለትን ሰው በችሎታ ማነስ ብሎ ማስወጣት ችሎታ ያነሰው ማን አንደሆነ የሚያውቅ ያውቀዋል፤ እነዚህን የተለያዩ ባለሙያዎች በማስወጣት ወያኔ ሰዎቹን አልጎዳም፤ ሁሉም የተሻለ ኑሮና የተሻለ የሥራ እርካታ አግኝተዋል፤ የተጎዱት መሥሪያ ቤቶቹ ናቸው፤ ከወያኔ ጋር ወደኋላ የሄደችው ኢትዮጵያ ነች፤ ወደኋላ የሄደው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።