Tuesday, February 4, 2014

አቡጊዳ – ከሳኡዲ የተለመሱ ተቃዉሞ ሊኦያሰሙ ሲሉ በፖሊስ ተበተኑ !


በሳዉዲ መንግስት በግፍና ጭካኔ ተባረው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የተደረጉ ኢትዮጵያዊያን በአዲስ አበባ፣ በዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ፊት ለፊት ፣ «መንግስት ትኩረት አልሰጠንም» በሚል ድምጻቸውን ለማሰማት የተሰባሰቡ ወደ 400 መቶ የሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን በፖሊሲ እንዲበተኑ መደረጉን የአንድነት ፓርቲ ልሳን የሆነው የፍኖት ጋዜጣ ዘገበ።

«ቦሌ አካባቢ ከሚገኘው ጊዜያዊ ማረፊያቸው፣ ከ400 በላይ ሆነው ቅሬታቸውን ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ለማሰማት ያቀዱትን ቅሬታ አቅራቢዎች ፖሊስ በትኗቸዋል፡፡ ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መሀከል ከ20 የማይበልጡት ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አቅራቢያ ቢሰባሰቡም ፖሊሶች አከባቢውን ለቀው እንዲሄዱ እያስገዷቸው መሆኑን በስፍራው ያለው የፍኖተ ነፃነት ሪፖርተር ዘግቧል» ሲል ነበር ፍኖት የዘገበዉ።
የሳዉዲ ስደተኞች ወደ አገራቸው ተመልሰው በነበረ ጊዜ፣ ባለስልጣናቱ ከነርሱ ጋር ፎቶ በመነሳት፣ ለስደተኞች የሚያስፈልገው እንክብካቤ እንደሚደረግ ሲገጽሉ እንደነበረ ይታወቃል። ኢቲቪ ስደተኞችን በአይሮፕላን ማረፊያ ቃለ መጠይቅ በማድረግ፣ ብነስደተንጮ የተሰጡ የምስጋና መልእክቶችን በማስተላለፍ፣ የስደተኞችን ጉዳይ ለፖለቲካ መጠቀሚያ አድርጎት እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነዉ።

No comments:

Post a Comment