Wednesday, January 29, 2014

የኢትዮጵያ መንግስት የግንቦት7 መሪዎችን ኮምፒዩተሮች በዘመናዊ የስለላ መሳሪያዎች ሲሰልል እንደተደረሰበት አንድ አለማቀፍ ተቋም አጋለጠ

ጥር ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህዝቦችን ደህንነት ከመንግስታት ጥቃት ለመከላከል የተቋቋመው ፕራይቬሲ ኢንተርናሽናል የተባለው  ተቋም ለእንግሊዝ መንግስት የገቢዎቸና ጉምሩክ መስሪያ ቤት በጻፈው ደብዳቤ “ጋማ ኢንተርናሽናል የተባለው የእንግሊዝ ኩባንያ በአለም ላይ የሰብአዊ መብቶችን በመጣስ ለሚታወቁ አገሮች ኮምፒይተሮችን፣ የሞባይልና የስካይፕ የስልክ ግንኙነቶችን እንዲሁም የኢሜል ልውውጦችን በርቀት ሆኖ ለመከታተል የሚያስችለውን ፊን ፊሸር ወይም ፊን ስፓይ በሚል ስም የሚጠራውን የመሰለያ መሳሪያ ከአውሮፓ ህብረት ውጭ ላሉ አገሮች በመሸጥ ዜጎች እንዲሰለሉና ደህንነታቸው አደጋ ላይ እንዲወድቅ በማድረጉ  ምርመራ እንዲጀመር” ሲል ጠይቋል።

የታመቀው የኢትዮጵያውያን ምሬት፡ የሕይወት ማሽቆልቆልና በፍርሃት መሽማቀቅ አፋጣኝ መፍትሄ ይሻል


ኢትዮጵያ በሕወሃት ዘመነ አመራር የታወቀችባቸው ብዙ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። ብዙ “እንዴ!”የሚይሰኙ ጥሩ አሳቦችም ፈልቀዋል – አፈጻጸማቸው እትይለሌ ቢሆንም። ከነዚህም መካከል መሠረተ ልማት፡ በጤናና በትምህርት መስኮች መሻሻሎች መታየታቸው ወዘተ መልካም ይነገርላቸዋል – የቢል ጌትስን የራስ ተጠቃሚነትና ኢምፓየር ግንባታ ወደጎን ትተን! በዕጦት ደረጃም በሀገራችን የስብዓዊ መብቶች አለመክበር፣ የፍትህ አለመኖርና ለአብዛኛው ሕዝባችን የምግብ ዕጦት ዋና ዋና ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው።
Prime Ministers Katainen and Hailemariam (Credit: ERTA)
Prime Ministers Katainen and Hailemariam (Credit: ERTA)
ለምሳሌም ያህል፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 30 ስላማዊ ስልፍ የማድረግንና መንግስትን መቃወምን ግልጽ ቢያደርግም፡ እሁድ ዕለት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመሰጠት ለመቃወም: ለሚመለተው አሳውቀው ስላማዊ ስልፍ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ሲሉ የአዘጋጁ የስማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት ጎንደር ውስጥ ተይዘው ታስረዋል። በተመሳሳይ መንገድ ትግራይ ውስጥም የአረና አመራሮች ሕዝቡን ቀሰቀሳችሁ በሚል ውንጀላ አዲግራት ውስጥ አመራሩና አባሎቹ ክፉኛ ተደብድበዋል – ጉዳት የደረሰባቸውም ሕክምና ለመሻት ተገደዋል። ይህንኑ አስመልክቶ፡ አንዱ ተደብዳቢ መምህር አብርሃ ደስታ የሚከተለውን ጽፏል፡

በአንጀሊና ጆሊ ኤክስኪዩቲቭ ፕሮዲዩሰርነት የተሰራው ኢትዮጵያዊው “ድፍረት” መነጋገሪያ ሆኗል

A+AA-
በአንጀሊና ጆሊ ኤክስኪዩቲቭ ፕሮዲዩሰርነት  የተሰራው ኢትዮጵያዊው “ድፍረት” መነጋገሪያ ሆኗል

በአንጀሊና ጆሊ ኤክስኪዩቲቭ ፕሮዲዩሰርነት የተሰራው ኢትዮጵያዊው “ድፍረት” መነጋገሪያ ሆኗል

‘አንጀሊና ጆሊ’ የሚለው ስም፣ አሁንም ከኢትዮጵያ ጋር ተያይዞ ተነሳ፡፡ አሁንም በስፋት ተዘገበ፣ በብዙዎች ተሰማ፣ ብዙዎችን አነጋገረ፡፡ አሁን ይሄን ታዋቂ ስም ከኢትዮጵያ ጋር አያይዞ ያስነሳው፣ ያ የፈረደበት ማደጎ አይደለም፡፡ በሁለቱ መካከል ትስስር የፈጠረችው፣ ከአመታት በፊት ወደ አሜሪካ በማደጎ የተወሰደችው ዘሃራ አይደለችም - አበራሽ እንጂ፡፡ ከአዲስ አበባ ወጣ ብላ በምትገኝ አንዲት የገጠር መንደር ውስጥ ተወልዳ ያደገች የ14 ዓመት ልጃገረድ ናት- አበራሽ በቀለ፡፡
አበራሽንና አንጀሊናን ምን አገናኛቸው?... ህይወት!...
ከአመታት በፊት…
የገጠሯ ጉብል አበራሽ፣ አንድ ማለዳ ደብተሮቿን ሸክፋ ከጎጆዋ በመውጣት፣ ከመንደሯ ርቆ ወደሚገኘው ትምህርት ቤቷ የእግር ጉዞ ጀመረች፡፡ ዳገት ቁልቁለቱን እየወጣች እየወረደች ወደ እውቀት ቤቷ ፈጥና ለመድረስ ረጅሙን መንገድ ተያያዘችው፡፡ እንዳሰበችው ፈጥና ለመድረስ፣ ድካሟን ተቋቁማ ነጠቅ ነጠቅ ብላ መራመድ ይኖርባታል፡፡ ምክንያቱም ትምህርት ቤቷ ለመድረስ ገና ብዙ መንገድ ይጠብቃታል። ምክንያቱም እሷ እንደ ሰውየው ፈረስ የላትም - ዳንግላሳ እየጋለበ ከጥሻው ስር ብቅ ሲል እንዳየችው ሰውዬ!!...

Sunday, January 26, 2014

የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ

“ኦክስፋም” በመልካም ሥራቸው ከታወቁ ትላልቅ ዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ነው። በቅርቡ አንድ መቶ ሀያ አምስት አገሮችን ያካተተ ከምግብ አቅርቦትና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ አራት ዝርዝርና አንድ አጠቃላይ አመላካቾች አሉት።
1. አመላካች አንድ: የምግብ እጥረት
ይህ አመላካች “በየአገሮቹ ምን ያህል ለበላተኛው የሚበቃ ምግብ አለ?” የሚለውን ይለካል። በጥናቱ ውጤት መሠረት በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ የመጨረሻዎቹ አስር አገሮች የሚከተሉት ናቸው: – ቡሩንዲ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ ናይጄሪያ፣ ላኦስ፣ ባንግላዴሽ፣ መካከለኛዉ አፍሪካ ሪፑብሊክ እና ህንድ። ኢትዮጵያ አገራችን ከመጨረሻ አራተኛ ናት።

Friday, January 24, 2014

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከ250 በላይ ሰዎችን አሰረ

ኢሳት ዜና :-ኮሚሽኑ ተጠርጣሪዎቹ የተሳሩት በአዲስ አበባ የተለያዩ ክፍለከተሞች በመኪና ስርቆት፣ ማጅራት በመምታትና ሌሎች ወንጀሎች መፈጸማቸውን ጥናት ካካሄድኩ በሁዋላ ነው ብሎአል።

ተያዙ የተባሉት ተጠርጣሪዎች ፍድር ቤት ስለመቅረባቸው ኮሚሽኑ ያስታወቀው ነገር የለም።

የእነ አንዱዓለም አራጌ ቀጠሮ ተምታታ

ፍርድ ቤቱ ለጥር 30 ቀጥሯቸዋል፤ ሬጅስትራር በበኩሉ ጥር 24 ቀን 2006ዓ.ም መቅረብ አለባቸው ይላል፤

በነአቶ አንዱአለም አሬጌ ስም ያለው የክስ መዝገብን በሚመለከት በፌዴራል ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከተከሳሽ ጠበቆችና ከቤተሰቦች ጋር ብንቀርብም ፍርድ ቤቱ ቀጠሮው ትላንት ስለ ማለፉ ተናግሯል። የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው አጀንዳቸው ላይ የያዙት ዛሬ ጥር 16 ቀን 2006 ዓ.ም መሆኑን ቢገልፁም በዳኛ አዳነ ንጉሴ፣ ዓሊ መሐመድ፣ አልመው ወሌ እና ሙስጠፋ አህመድ የተሰየመው ችሎት በበኩሉ የቀጠሮው ቀን ትላንት ማለፉን ተናግረዋል።